25ኛ አመቱን ለማክበር በዝግጅት ላይ የሚገኘው፤ ፍቅረ ሰላም አጠቃላይ ሆስፒታል ያለ ጊዜያቸው የተወለዱ ጨቅላ ሕጻናትን በተመለከተ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብር አካሄዷል፡፡
ፍቅርሰላም ሆስፒታል 25 ዓመቱን ሲያከብር ከሚያከናውናቸው 25 በጎ ነገሮች አንዱ፤ በህዳር 20 – 2018 ዓ.ም መርሀ ግብር እንደሆነ ተነግሯል።
ሆስፒታሉ ባለፈው ሐሙስ የደም ልገሳ አሰባስቦ የነበረ ሲሆን፤ የሆስፒታሉ መሥራች ዶክተር ፍቅረማሪያም ጉደታ ማህበራዊ ኃላፊነት መወጣት ትልቁ ሥራችን ነው ብለዋል።
በመርሃ ገብር የተገኙት የጨቅላ ሕጻናት ሠብ ስፔሻሊስት የሆኑት ዶክተር ሙሉዓለም ገሠሠ በበኩላቸው፤ ያለጊዜ መወለድ በልዩ ልዩ ምክንያቶች የሚያጋጥም መሆኑን ገልጸዋል። አክለውም፤ በጉዳዩ ላይ የባለሙያ ምክርና ግንዛቤ ለወላጆች እና ለህብረተሰቡ ማስያዝ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል።
ሆስፒታሉ ከሕክምና አገልግሎት ጎን ለጎን የተለያዩ በጎ አድራጎት ሥራዎችን እየሰራ እንደሚገኝና ይህን ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
ፍቅረሰላም አጠቃላይ ሆስፒታል ከተመሠረት 25 ዓመቱን ያስቆጠረ ሲሆን፤ በ3 ሰራተኛ የጀመረው ሆስፒታሉ አሁን ላይ 250 ለሚደርሱ ሰዎች የሥራ ዕድል መፍጠሩ ተገልጿል።
(አሐዱ ሬዲዮ)
