አሐዱ ባንክ የምስረታ በዓሉን በሰሊሆም የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል አከበረ

Date:


አሐዱ ባንክ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሕጋዊ ሰውነት ያገኘበትንና ፤ የባንኩን የምስረታ ጉባኤ ያከናወነበትን እለት ምክንያት በማድረግ ፤ በሰሊሆም የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል የምሳ ማብላት መርሀ-ግብር አከናውኗል።

ባንኩ ከብሔራዊ ባንክ የሕጋዊ ሰውነት እውቅና ያገኘበትንና ፤ የባንኩን የምስረታ ጉባኤ ያከናወነበትን ቀን ምክንያት በማድረግ ፤ በየዓመቱ የተለያዩ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን የሚወጣበት ስራዎችን እንደሚሰራ የአሐዱ ባንክ የማርኬቲንግ እና የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር የሆኑት አቶ አብይ ተናግረዋል።

በዚህም ዘንድሮ የታህሳስ 24 ቀን የምስረታ በአሉን በማስመልከት ፤ ለተለያዩ የበጎ አድራጎት ተቋማት የገንዘብና የአይነት ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ የተናገሩት ዳይሬክተሩ ፤ ከእነዚህም ውስጥ አንዱ በሆነው በሰሊሆም የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል በመገኘት ፤ በማዕከሉ ለሚገኙ የአዕምሮ ህሙማን ለሁለት ቀን የሚቆይ የምሳ ማብላት መርሀ-ግብር ማስጀመሩን አስታውቀዋል።

አሐዱ ባንክ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት በኩል የበጎ አድራጎት ስራውን አሁንም አጠናክሮ እንዲቀጥል የገለፁት ዳይሬክተሩ ፤ በዚህ ሳምንት ከሚደረጉት ስራዎች መካከልም በመቄዶንያ የአዕምሮ ህሙማንና የአረጋውያን መርጃ ማዕከል ተመሳሳይ መርሀግብር እንደሚያካሂድ ተገልፀዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...