አየር መንገዱ ለቦርድ አባላቱ ሽኝት አደረገ

Date:

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቀድሞ የአየር መንገዱ ቦርድ አባል ለነበሩት ክቡር የኢ.ፌ.ዲ. ሪ ፕሬዝደንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ የሽኝት መርሐ ግብር አካሄደ።


በዚህ የሽኝት መርሀግብር ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ቦርድ ሰብሳቢ ክቡር ሌ/ጄኔራል ይልማ መርዳሳ፣ የቦርድ አባላት፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከፍተኛ የአመራር አባላት ተገኝተዋል።


በመርሀግብሩ ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ባስተላፉት መልዕክት አየር መንገዱ አህጉራዊ መሪነቱን እና አለም አቀፋዊ ተወዳዳሪነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል እንዲሁም እንደወትሮው ሁሉ የጥንካሬ የእድገት እና የአዳዲስ ዕመርታዎች ተምሳሌት ሆኖ እንዲዘልቅ ክቡር ፕሬዝደንት በቦርድ አባልነታቸው ላበረከቱት አስተዋፅዖ ምስጋና አቅርበዋል።


በተመሳሳይም አየር መንገዱን በቦርድ አባልነት ያገለገሉት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ ክብርት ወሮ ያስሚን ወሀብረቢ ሽኝት ተደርጎላቸዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...