አየር መንገዱ ለቦርድ አባላቱ ሽኝት አደረገ

Date:

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቀድሞ የአየር መንገዱ ቦርድ አባል ለነበሩት ክቡር የኢ.ፌ.ዲ. ሪ ፕሬዝደንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ የሽኝት መርሐ ግብር አካሄደ።


በዚህ የሽኝት መርሀግብር ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ቦርድ ሰብሳቢ ክቡር ሌ/ጄኔራል ይልማ መርዳሳ፣ የቦርድ አባላት፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከፍተኛ የአመራር አባላት ተገኝተዋል።


በመርሀግብሩ ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ባስተላፉት መልዕክት አየር መንገዱ አህጉራዊ መሪነቱን እና አለም አቀፋዊ ተወዳዳሪነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል እንዲሁም እንደወትሮው ሁሉ የጥንካሬ የእድገት እና የአዳዲስ ዕመርታዎች ተምሳሌት ሆኖ እንዲዘልቅ ክቡር ፕሬዝደንት በቦርድ አባልነታቸው ላበረከቱት አስተዋፅዖ ምስጋና አቅርበዋል።


በተመሳሳይም አየር መንገዱን በቦርድ አባልነት ያገለገሉት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ ክብርት ወሮ ያስሚን ወሀብረቢ ሽኝት ተደርጎላቸዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት በዛሬ ዕትሟ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ነሔሴ 16 2018 ዓ.ም ገበያ...

ቱርክ ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ የእስር ማዘዣ አወጣች

ቱርክ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ ዓለም አቀፍ...

በመቀለ የሚካሄደው የአሸንዳ በዓል የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ተሰረዘ

በትግራይ በርካታ ታዳሚ በሚገኝበት በየዓመቱ የሚከበረው የአሸንዳ ባህላዊ በዓል...

የኢትዮጵያ ፖስታ 3 ሺሕ የሚጠጉ ቅርንጫፎቹን ወደ ባንክ ኤጀንትነት ለመቀየር እንቅስቃሴ ጀመረ

የኢትዮጵያ ፖስታ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ 3 ሺሕ በሚጠጉ ቅርንጫፎቹ...