በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ዳግም ጦርነትእንዳይቀሰቀስ ዲፕሎማቶች አሳሰቡ

Date:

በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ዳግም ጦርነት እንዳይቀሰቀስ ከወዲሁ መግታት እንደሚገባ የአሜሪካና አውሮፓ ዲፕሎማቶች አሳሰቡ፡፡

የአፍሪካ ቀንድ ምክትል ልዩ መልዕክተኛ የነበሩት ፓይተን ኖፍ እና የቀይ ባህር የጥናት ማዕከል ሊቀመንበር አሌክሳንደር ሮንዶስ፣ በሁለቱ ጎረቤት ሀገራት መካከል የሚስተዋለውን ውጥረት አስመልክተው፣ ፎሬይን ፖሊሲ መጽሔት ላይ ሀሳባቸውን አጋርተዋል፡፡

በሁለቱም በኩል የሚስተዋሉ የቃላት ልውውጦችና የጦርነት ዝግጅቶች በሀገራቱ መካከል ጦርነት ሊቀሰቀስ እንደሚችል አመላካች እንደሆኑ ዲፕሎማቶቹ ጠቁመዋል፡፡

በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ያለው ፍጥጫ ወደ ጦርነት የሚያድግ ከሆነ ሰሜን ምስራቅ አፍሪካንና በጂኦፖለቲካዊ ጠቀሜታው ወሳኝ የሆነው ቀይ ባህር ላይም ችግር ሊጋርጥ እንደሚችል አመልክተዋል፡፡

አለም በሰፊ አህጉራዊና አለምአቀፋዊ ስርዓት አልበኝነት እየተናጠች በምትገኝበት በዚህ ወቅት፣ በትግራይ ያለው የፖለቲካና የጸጥታ ሁኔታ መበላሸት በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ጦርነትን ሊያስከትል እንደሚችልም አሳስበዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር፤ ለወረራ የታለመ ማደናገሪያ? ሩሲያ ማስጠንቀቂያ ሰጠች!

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ውጥረትን ለመቀነስ...