ኢትዮጵያ እና ፈረንሳይ የኢኮኖሚ ማሻሻያን የሚደግፍ ስምምነት ተፈራረሙ

Date:

የኢትዮጵያና የፈረንሳይ መንግስታት የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ማሻሻያ የሚደግፉ ታሪካዊ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል።

ስምምነቱን የኢትዮጵያ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ እና በፈረንሳይ የአውሮፓና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሚስዝ ኤሌኖሬ ካሮይት ተፈራርመዋል።

ስምምነቱ የዕዳ ሽግሽግ (Debt Restructuring): በG20 የጋራ ማዕቀፍ ስር ከሁለትዮሽ አበዳሪዎች ጋር የተደረገ የመጀመሪያው ታሪካዊ የዕዳ ሽግሽግ ስምምነት ተፈርሟል።

እንዲሁም ለሁለተኛው የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ (HGER 2.0) ማስፈጸሚያ የሚውል 80 ሚሊየን ዩሮ የበጀት ድጋፍ እና 1.5 ሚሊየን ዩሮ የቴክኒክ ድጋፍ ስምምነት መደረጉን ኢቢሲ ዘግቧል።

በተጨማሪም ፈረንሳይ በኢትዮጵያ በሚገነባው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ላይ ለመሳተፍ ፍላጎት አሳይታለች።

በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ያለው የፈረንሳይ አጠቃላይ የኢንቨስትመንት መጠን ከ600 ሚሊየን ዩሮ በላይ የደረሰ ሲሆን፥ ከዚህ ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆነው (300 ሚሊየን ዩሮ) ለኢነርጂ ዘርፍ መዋል መቻሉ ተገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...