አየር መንገዱ ሦስት አዳዲስ የአገር ውስጥ አውሮፕላን ማረፊያዎችን ሊያስመርቅ ነው

Date:

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በግንባታ ላይ ከሚገኙት የአገር ውስጥ የአውሮፕላን ማረፊያዎች መካከል ሦስቱ ተጠናቀው በሚያዚያ ወር አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምሩ አስታወቀ።

አየር መንገዱ ባወጣው መረጃ መሠረት፣ የአገሪቱን የአየር ትራንስፖርት ተደራሽነት ለማስፋፋት እየተገነቡ ካሉ ፕሮጀክቶች ውስጥ ነገሌ ቦረና ፣ ጎሬ መቱ ፣ ደብረ ማርቆስ ፕሮጀክቶቹ ተጠናቀው በመጪው ሚያዚያ ወር 2018 ዓ.ም ይመረቃሉ።

አዳዲሶቹ ማረፊያዎች የንግድ እና የማኅበራዊ ትስስርን ከማጠናከራቸው ባለፈ፣ ለተጓዦች አማራጭና ቀልጣፋ ትራንስፖርት ለማቅረብ ያለሙ ናቸው።

አየር መንገዱ ከእነዚህ ሦስት ማረፊያዎች በተጨማሪ ሌሎች የኤርፖርት ግንባታዎችንና የማስፋፊያ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።

“የእነዚህ አየር ማረፊያዎች መጠናቀቅ አየር መንገዱ ያለውን የአገር ውስጥ በረራ መዳረሻዎች ቁጥር ከማሳደጉም በላይ፣ ለየአካባቢው ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል” ሲል አየር መንገዱ አመልክቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጥቃት አድራሹ ከካሊፎርኒያ መሆኑን ትራፕ ገለፁ

ትናንት ቅዳሜ ምሽት በዋይት ሃውስ የጋዜጠኞች ማኅበር የእራት ግብዣ...

በኬንያ የመንገደኞች አውሮፕላን ከመስመሩ ወጥቶ ተከሰከሰ

ዛሬ ረፋድ ላይ በኬንያ ማንዴራ የአውሮፕላን ማረፊያ አንድ...

አቶ ጀማል አህመድ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ተጨማሪ 26 ሚሊየን ብር ሰጡ

አቶ ጀማል አህመድ ባሳለፍነው ወር ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ  ከሰጠው...

“የቻይና-አፍሪካ የምርምር ማዕከል”በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሊከፈት ነው

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከቻይና-አፍሪካ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር "የቻይና-አፍሪካ የምርምር...