የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ በጅቡቲ ተሸለመ

Date:

የጅቡቲ ትራንዚተርስ አሶሴሽን የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ (ኢባትሎ) በሎጂስቲክስ ዘርፍ ላበረከተው ዓይነተኛ አስተዋጽኦ እና አጋርነት ሽልማት ማበርከቱ ተነግሯል ።

ትናንት በጅቡቲ አምባሳደሮችና የዘርፉ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት በተደረገው የዕውቅና አሰጣጥ ፕሮግራም ላይ ማህበሩ ላለፉት ዓመታት በነበረን የአብሮነት ጉዞ በስራ አጋርነት ላሳያችሁት ድንቅ ብቃትና ዘላቂ ወዳጅነት ለኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ያለንን ክብር እንገልፃለን ሲል ሸልማቱን መስጠቱን ነዉ የተገለጸው ።

የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ክቡር በሪሶ አመሎ (ዶ/ር) እንደተናገሩት በሎጂስቲክስ ዘርፍ ባለን የጋራ ስራ የጭነት ምጣኔን ከፍታ በማረጋገጥና ገቢያችንን በማሳደግ፣ ግንኙነታችንን በማጠናከር፣ የስራ ፈጠራን በማስፋት፣ የሰራተኞቻችንን ጤናማነት በማረጋገጥ ለጠንካራ የኢኮኖሚ ግንባታ መረጋገጥ እና የሁለትዮሽ ተጠቃሚነት እናውለዋለን ብለዋል፡፡

ይህ ሽልማት የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ድርጅት በክልሉ የሎጂስቲክስ ዘርፍ እያበረከተ ያለውን አስተዋጽኦ የሚያሳይ ሲሆን፣ የሁለቱ አገራት የትብብር ግንኙነት ወደፊትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ይጠበቃል ተብሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...