የምግብ ዘይት ፋብሪካዎች በፋይናንስ እና ግብዓት እጥረት 50 በመቶ ብቻ እየተጠቀሙ ነዉ

Date:

በኢትዮጵያ የሚገኙ የምግብ ዘይት አምራች ፋብሪካዎች በፋይናንስ እና በግብዓት እጥረት ምክንያት ከማምረት አቅማቸው 50 በመቶውን ብቻ እየተጠቀሙ መሆኑን የኢትዮጵያ የምግብ ዘይት አምራቾች ማኅበር አስታውቋል።

ማኅበሩ  እንደገለጸው፤ ዘርፉ ከፍተኛ ፋይናንስ የሚጠይቅ ቢሆንም በቂ በጀት እና የጥሬ ዕቃ አቅርቦት ባለመኖሩ ኢንዱስትሪዎች በሙሉ አቅማቸው ማምረት አልቻሉም።

የማኅበሩ ሥራ አስኪያጅ አቶ ትልቅሰው ለታ፣ ፋብሪካዎቹ በሙሉ አቅማቸው አለማምረታቸው የምርት እጥረት እንዲከሰት ፣ የዋጋ ጭማሪ እንዲኖር እና የገበያ አለመረጋጋት እንዲፈጠር ማድረጉን ገልጸዋል።

የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል በበኩላቸው፣ የዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ካለፉት ዓመታት መሻሻል ቢያሳዩም አሁን ካለው የገበያ ፍላጎት አንጻር አቅርቦቱ ገና አለመመጣጠኑን አረጋግጠዋል።

ችግሩን ለመፍታት እና አምራቾች እንዲበረታቱ የማድረግ ሥራ እየተሠራ መሆኑን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። በተለይም የፋብሪካዎች የማምረት አቅም እንዲጎለብትና ተመጣጣኝ የገበያ አቅርቦት እንዲኖር ትኩረት መሰጠቱን አብራርተዋል።

የሀገር ውስጥ ዘይት አምራቾችን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር መንግሥት ከአበዳሪ ተቋማት ጋር በመሆን በቂ ብድር እንዲመቻች እና ፋብሪካዎች በሙሉ አቅማቸው እንዲያመርቱ ምቹ ሁኔታ መፈጠር እንደሚገባው ተመላክቷል።

(አሐዱ ራድዮ)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...

ከ 50 ሚሊዮን በላይ መራጮች በማንዋልና በዲጂታል ተመዝግበዋል

ከየካቲት 28_መጋቢት 28 የመራጮች ምዝገባ ሲካሄድ እንደነበር ይታወቃል። በተለያዩ ጉዳዮች...