“በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ” ዓለም አቀፍ ፎረም  ሊካሄድ ነው

Date:


‎ኢትዮጵያ ለኢንቨስትመንት ያላትን ዝግጁነት ለዓለም የምታበስርበት 4ኛው “በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ” ዓለም አቀፍ ፎረም በመጋቢት ወር አጋማሽ በአዲስ አበባ ሊካሄድ ነው።

‎የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ከገንዘብ ሚኒስቴርና ከልማት አጋሮች ጋር በመተባበር መጋቢት 17 እና 18 ቀን 2018 ዓ.ም በሚያካሂደው በዚህ ታላቅ መድረክ ላይ፣ ከ800 በላይ ዓለም አቀፍ ባለሀብቶች፣ የንግድ መሪዎችና ፖሊሲ አውጪዎች ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

‎ኮሚሽነር ዶክተር ዘለቀ ተመስገን እንደገለጸው በባለፈው 3ኛው ፎረም በማዕድንና በሶላር ኢነርጂ ዘርፍ የተሰማሩ አምስት ድርጅቶች በ1.6 ቢሊየን ዶላር ስምምነት ተፈራርመው በአሁኑ ወቅት ሙሉ ለሙሉ ወደ ሥራ የገቡ ሲሆን፤ በዘንድሮው 4ኛው ፎረም ደግሞ ከ2.6 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር በላይ የሚያወጡ አዳዲስ የኢንቨስትመንት ስምምነቶች እንዲፈረሙ እቅድ ተይዟል።

‎ይህ ፎረም የንግድ ለንግድ ትስስርን ከመፍጠር ባለፈ፣ ኢትዮጵያ ለውጭ ኢንቨስትመንት ያላትን ምቹ የፖሊሲ ከባቢና የልማት ዕድሎች ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በተግባር የምታሳይበት ወሳኝ መድረክ እንደሚሆን ይታመናል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...

ከ 50 ሚሊዮን በላይ መራጮች በማንዋልና በዲጂታል ተመዝግበዋል

ከየካቲት 28_መጋቢት 28 የመራጮች ምዝገባ ሲካሄድ እንደነበር ይታወቃል። በተለያዩ ጉዳዮች...