የአበበች ጎበናን ህይወት የሚተርክ ፊልም ተመረቀ

Date:

የአበበች አደራ” በሚል ስያሜ እንዲሁም “ፍቅር፣ ርህራሄ፤ ወደር የማይገኝለት ሰብዓዊነት!”በተሰኘ መሪ ቃል ህይወት የሚተርክ ፊልም ምርቃት እና ገቢ ማሰባሰቢያ መርሐግብር  በትናትናዉ  እለት ተካሄዷል።

መርሐ ግብሩ ክብርት ዶክተር አበበች ጎበና የሚታወሱባቸውንና ትውልድ ሊያውቀውና ሊማርበት የሚገባ የህይወታቸው እሴቶችና መርሆዎችን ለማስገንዘብ እንዲሁም ለትውልድና ለኢትዮጵያ መንግስት አደራ ሰጥተው የሄዱትን ድርጅት ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ ነው፡፡

የክብር ዶክተር አበበች ጎበና የአበበች ጎበና ቻሪቲ መስራችና ባለራዕይ ሲሆኑ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ህፃናትን በማሳደግና በአያሌ የሰብዓዊነት ተግባራቸው በመላው ዓለም እውቅናን ያገኙ ሰው ናቸው፡፡

በ1972 ዓ.ም ወላጆቻቸው በረሀብ የሞቱባቸው ሁለት ህፃናትን በማንሳት የተጀመረው ጉዞ ከአርባ ሰባት ዓመታት በኋላ እንኳ ብዙዎች የሚጓዙበት የርህራሄና የሰብዓዊነት ጎዳና ሆኖ ቀጥሏል፡፡

ከአመታት በፊት በኮሮና ወረርሽኝ ሳቢያ ህይወታቸው ያለፈው እኒህ ታላቅ እናት በስራ ወዳድነታቸው፤ በደግነታቸውና በሰብዓዊ ተግባራቸው በትውልዶች ይታወሳሉ፡፡ ስራቸውም በአያሌ ልጆቻቸውና የልጅ ልጆቻቸው ህያውነት ውስጥ ተጠብቆ ይኖራል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚያደርጉት ድርድር እስኪጠናቀቅ ድረስ የተኩስ አቁሙ መራዘሙን አስታወቁ

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፓኪስታን ጥያቄ መሠረት ከኢራን ጋር የገቡትንየተኩስ...

ለኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ የሚውል የ40 ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ተፈቀደ

የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የልማት ክንፍ የሆነው ኢአይቢ ግሎባል (EIB...

ሃይንከን በአልኮል መጠኑ ጠንከር ያለ ቢራ ለኢትዮጵያ ገበያ አስተዋወቀ

ሃይንከን ኢትዮጵያ በእለም አቀፍ ደረጃ ዝነኛ የሆነውን ዴሰፔራዶስ (Desperados)...