ታሜሶል ኮምኒኬሽን የአዲስ አመት ዋዜማ ኤግዚቢሽንን በተከታታይ ማስተናገድ የሚያስችለውን ጨረታ አሸነፈ

Date:

የ2018 አዲስ አመት ዋዜማ ኤግዚቢሽንን ለማዘጋጀት ዛሬ መጋቢት 16 ቀን በተከፈተው ጨረታ ታሜሶል ኮምኒኬሽን በ92 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር አሸናፊ ሆነ፡፡

በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማእከል የተዘጋጀውን የ2017 የአዲስ አመት ዋዜማ ያዘጋጀው ታሜሶል ቀጣዩን የአዲስ አመት ዋዜማ ለማስተናገድ ያቀረበው ዋጋ ከተከታዩ ተጫራች አንፃር የ6.9 ሚሊየን ብር ብልጫ አለው፡፡

በቀጣዮቹ ቀናት የሚከፈተውን የፋሲካ በዓል ዋዜማ ኤክስፖ ጨረታ በ60 ሚሊየን ብር አሸንፎ የሚያዘጋጀው ታሜሶል ኮምኒኬሽን አዳዲስ አቀራረቦችን በማስተዋወቅ የበዓል ዋዜማ ግብይቱ የተሻለ እና ሳቢ እንዲሆን እንደሚሰራ ነው ለካፒታል የገለጸው፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የሳህለወርቅ ዘውዴ አዲሱ አለም አቀፍ ሹመት በተመድ ልዩ ተልእኮ ተሰጣቸው

የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ወይዘሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በተመድ ዋና ፀሀፊ...

በሳዑዲ በምሕረት የተለቀቁ 320 ኢትዮጵያውያን

በሳዑዲ አረቢያ የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ የምህረት አዋጅ ከተሰጣቸው 1...

አሜሪካ እና እስራኤል ደቡብ ሊባኖስን ለአገሪቱ ጦር የማስረከብ ዕቅድ

አሜሪካ ድጋፏን በሰጠችው ዕቅድ መሠረት እስራኤል እና ሊባኖስ፤ የደቡብ...

የመሬት ልማትና አስተዳደር በበጀት ዓመቱ 63 በመቶ ያህሉን ማሳካት አልቻለም

የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ሊገባደድ በተቃረበው በጀት ዓመት ለመሰብሰብ...