ኢራን የሆርሙዝ ወሽመጥን “ለነዳጅ እና ጋዝ ላኪዎች ሙሉ በሙሉ ለመዝጋት” ዛተች

Date:

በኢራን እና በአሜሪካ መካከል የተኩስ ልውውጥ መደረጉን ተከትሎ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ የሆርሙዝ ወሽመጥን “ለነዳጅ እና ጋዝ ላኪዎች ሙሉ በሙሉ ለመዝጋት” ዛተ።

በባሕረ ሰላጤው አካባቢ ሁለቱ አገራት የተኩስ ልውውጥ ካደረጉ በኋላ እስላማዊ አብዮታዊ ዘቡ በሰጠው ማስጠንቀቂያ የሆርሙዝ ወሽመጥ ለነዳጅ እና ለጋዝ ላኪዎች ሙሉ በሙሉ ቢዘጋ “ኃላፊነቱን የምትወስደው አሜሪካ ናት” ብሏል።

አሜሪካ “እኩይ ድርጊቷን ከቀጠለች” ለሚወስደው እርምጃ ኃላፊነቱን እንደምትወስድም አስታውቋል።

የአሜሪካ ጦር ኢራን ወደ ሆርሙዝ ወሽመጥ የተኮሰቻቸውን አራት ድሮኖች መትቶ መጣሉን አስታውቋል።

የአሜሪካ ጦር ማዕከላዊ ዕዝ፤ ጎሩክ እና ቃሽም በተባሉ ደሴቶች ላይ የኢራን የባሕር ዳርቻ ጥበቃ ማዕከላት ላይ ጥቃት መፈጸሙን ገልጿል።

ኢራንም በአጸፋው በኩዌት የሚገኙ ሁለት የአሜሪካ ጦር መቀመጫዎች ላይ ባለስቲክ ሚሳዔል ተኩሳለች። በባሕሬን በሚገኘው የአሜሪካ ጦር ሰፈር ላይም ጥቃት ማድረሷ ተገልጿል።

የባሕሬን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ኢራን ያደረሰችውን ጥቃት “በጽኑ” እንደሚያወግዝ አስታውቋል። በባሕሬን እንዲሁም በኩዌት ላይ የደረሰውን ጥቃት “ግልጽ ጸብ አጫሪነት” ብሎታል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...