ከመንግስት መ/ቤቶች የጠፉ ተሽከርካሪዎች መኖራቸው በኦዲት ተረጋገጠ

Date:

የፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የመስሪያ ቤቶችን የተሽከርካሪ አያያዝና ስምሪትን በተመለከተ ባካሄደው ምርመራ በተለያዩ መ/ቤቶች ዘጠኝ መኪኖች ከናካቴው ጠፍተዋል ብሏል፡፡

ተጨማሪ ስድስት ሞተር ብስክሌቶችም የጠፋባቸው መ/ቤቶችን አግኝቻለሁ ብሏል፡፡

የተቋማቱን ስም ግን በኦዲት ሪፖርቱ አልተጠቀሰም፡፡

በሌላ በኩል የባለቤትነት መታወቂያ ደብተራቸው በሌሎች መ/ቤቶችና ድርጅቶች ስም ተመዝግቦ የተገኘ 595 የመንግስት ተሽከርካሪዎች በኦዲት ምርመራው ተገኝተዋል፡፡

እንዲሁም የሰሌዳ ቁጥር የሌላቸው 13 መኪኖች፣ 10 የሞተር ብስክሌቶችና 20 ትራክተሮች የንብረት አያያዛቸው በተፈተሹባቸው የመንግስት ተቋማት መገኘታቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት በሪፖርቱ ተናግሯል፡፡

ሌሎች 146 መኪኖች ፣ 27 ሞተር ብስክሌቶች፣ 18 የቁፋሮ መኪኖች ፣ 1 ሎደርና 1 ትራንክተር የሊብሬ ወይም የባለቤትነት መታወቂያ ደብተር ሊቀርብላቸው አልቻለም ተብሏል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመረጃ ነጻነት አዋጅን በሙሉ ድምፅ አጸደቀ

በምክር ቤቱ የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ እውነቱ...

በቬንዝዌላ በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ የ32 ሰዎች ህይወት አልፏል

በቬንዙዌላ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የታወጀ ሲሆን 7.2 እና 7.5...

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ “ሉሲ” ላገኟት ፕሮፌሰር የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጠ

የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ፥...

የሳህለወርቅ ዘውዴ አዲሱ አለም አቀፍ ሹመት በተመድ ልዩ ተልእኮ ተሰጣቸው

የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ወይዘሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በተመድ ዋና ፀሀፊ...