ፕሬዝዳንት ትራምፕ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ድርድር ለመጀመር መስማማታቸውን ገለጹ

Date:

በኢራን እና በአሜሪካ መካከል የሚደረገው ድርድር እንዲቀጥል መስማማታቸውን፤ ነገር ግን ቀደም ሲል የነበረው የተኩስ አቁም ማብቃቱን ለኢራን እንዳረጋገጡላቸው ፕሬዝዳንት ትራምፕ ተናገሩ።

“የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ ድርድሩን እንድንቀጥል ጠይቀውናል። እኛም ይህንን ለማድረግ ተስማምተናል” በማለት ፕሬዝዳንት ትራምፕ በትሩዝ የማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ ጽፈዋል።

አክለውም “ነገር ግን አሜሪካ ተደርሶ የነበረው የተኩስ አቁም ማብቃቱን በማያሻማ ሁኔታ አሳውቃቸዋለች” ብለዋል።

ለወራት የዘለቀውን ጦርነት ለማስቆም ሁለቱ አገራት ከሳምንታት በፊት የመግባቢያ ስምምነት ደርሰው ግጭቱ ጋብ ብሎ የነበረ ቢሆንም ካላፈው ማክሰኞ ጀምሮ አሜሪካ በከፈተችው ጥቃት ጦርነቱ ዳግም ተቀስቅሷል።

አሜሪካ እና ኢራን ድርድራቸውን ለመቀጠል መስማማታቸውን ትራምፕ ያሳወቁት ኳታር ከአሜሪካ ጋር በመቀናጀት አሸማጋዮችን ከአገሪቱ ባለሥልጣናት ጋር እንዲነጋገሩ ወደ ቴህራን ከላከች በኋላ ነው።

አንድ የአሜሪካ ባለሥልጣን ለሲኤንኤን እንደተናገሩት የትራምፕ አስተዳደር ስትራቴጂ በኢራን ላይ ጥቃት በመሰንዘር ግጭቱ እንዳይባባስ ጋብ በማድረግ ለዲፕሎማሲያዊ ጥረት በር መክፈት ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጠቅላይ መሪ ለአባታቸው ግድያ “የበቀል እርምጃ” እንደሚወሰድ ተናገሩ

የኢራን ጠቅላይ መሪ ሞጅታባ ኻሜኒ በጽሑፍ ባስተላለፉት መልዕክት አባታቸው...

የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን የመጨረሻ ልምምዱን ሰርቷል

ቡድኑ ነገ የአለም ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ ዙር የመልስ ጨዋታውን...

ኢራን ከአሜሪካ ጋር ለመደራደር አለመጠየቋን አስታወቀች

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋይ፤ አገራቸው...

ሱዳን ዉስጥ ለሦስት ዓመታት የተካሄደው ጦርነትን ሰለ ማቆም

የሱዳን ብሔራዊ ጦር ለሦስት ዓመታት የተካሔደውን ጦርነት ለማቆም አሜሪካ...