ኢራን በኦማን፣ ኩዌት፣ ባሕሬን እና ሶሪያ ውስጥ የሚገኙ የአሜሪካ ጦር ሰፈሮችን መምቷን አስታወቀች

Date:

  1. የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ኦማን ውስጥ የሚገኝ የአሜሪካ የባሕር ኃይል መከታተያ ራዳር ሥፍራዎችን እንዲሁም ኩዌት እና ባሕሬን ውስጥ የሚገኙ ዒላማዎችን መምታቱን አስታወቀ።
  2. ሶርያ ውስጥ የሚገኝ የአሜሪካ የልዩ ዘመቻ ዕዝ ማዕከል ላይም ጥቃት መፈጸሙን ገልጿል።ኦማን ውስጥ በተፈጸመው ጥቃት “የባሕር ኃይል የቁጥጥር ራዳር እና የአሜሪካ አየር መቆጣጠሪያ ራዳር” መመታታቸውን ዘቡ ባወጣው መግለጫ ጠቅሷል።
  3. “በኃይል የሚፈጸሙ የአጸፋ ዘመቻዎች ይቀጥላሉ። የሆርሙዝ ወሽመጥም በአብዮታዊ ዘቡ ባሕር ኃይል ቁጥጥር ሥር እንደሆነ ቀጥሏል” ብሏል።
  4. የአሜሪካ የልዩ ዘመቻ ዕዝ ማዕከል ላይ ተፈጽሟል በተባለው የሶርያው ጥቃት፤ “የራዳር ሥርዓት፣ በርካታ የልዩ ሄሊኮፕተሮች እና በርከት ያሉ አሜሪካውያን ኃይሎች” ዒላማ መደረጋቸውን ጠቅሷል።
  5. እንደ አብዮታዊ ዘቡ ገለጻ፤ በዮርዳኖስ ድንበር አቅራቢያ በሚገኘው አል ታንፍ የተፈጸመው ድንገተኛ ጥቃት፤ ከሁለት ቀናት በፊት በኢራናውያን ወታደሮች ላይ ለተፈጸመው ግድያ የአጸፋ እርምጃ ነው።
  6. ሶርያም ሆኑ አሜሪካ እስካሁን ተፈጸመ ስለተባለው ጥቃት አስተያየት አልሰጡም።የዮርዳኖስ ጦር ግን ወደ አገሪቱ የተወነጨፉ ሦስት የኢራን ሚሳዔሎችን ጉዳት ወይም ውድመት ሳይደርስ መትቶ መጣሉን አስታውቋል።
  7. ኢራን አብዮታዊ ዘብ አዲሱን ጥቃት ከመፈጸሙ አስቀድሞ አሜሪካ “በርካታ የኢራን ጦር ዒላማዎችን” መምታቷን ገልጻለች።
  8. ኢራን በበኩሏ ድልድዮች፣ ባቡር ጣቢያ እና የአየር ማረፊያን ጨምሮ በተለያዩ የሲቪል መሠረተ ልማቶች ላይ ጥቃት እንደተፈጸመባት አስታውቃለች።
  9. ሁለቱም አገራት የሚፈጽሟቸው ጥቃቶች እየተባባሱ ባሉበት በዚህ ወቅት፤ ወሳኙ የባሕር መተላለፊያ ሆርሙዝ ወሽመጥ በኢራን እንደተዘጋ ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጄኤፍኤም 106.7 የሬዲዮ ጣቢያ ለ6 ወራት ታገደ

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ባደረገው የይዘት ክትትልና የኢንስፔክሽን ምልከታ...

ሱልጣን ቢን ኻሊፋ ግሩፕ በኢትዮጵያ በሆቴል ዘርፍ ሊሰማራ ነው

በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች የኢፌዲሪ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር...

የአሜሪካ የታክስ ህግ የስፔንን የዓለም ዋንጫ ሽልማት ስጋት ላይ ጣለ

የስፔን ብሔራዊ ቡድን ከዓለም ዋንጫ ሊያገኘው ከሚችለው 50 ሚሊዮን...

ህወሓት ከሌሎች ተቃዋሚ ኃይሎች ጋር የሚደረግ ጥምረት አስፈላጊ መሆኑን ገለጸ

ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ...