⚡️
የአዲስ አበባ ከተማን የትራንስፖርት አገልግሎት ለማዘመን ከዓለም ባንክ ጋር ፍሬያማ ውይይት መደረጉን ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታወቁ።
ከንቲባዋ በዓለም ባንክ የኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ ሱዳን እና ደቡብ ሱዳን ዳይሬክተር ከሆኑት ማርያም ሳሊም ጋር በጋራ ለመስራት ተስማምተዋል።
የውይይቱ ዋና ዓላማ የከተማዋን ትራንስፖርት ማሻሻልና በተለይም “E-mobility” (የጭስ አልባ ትራንስፖርት) ተደራሽነትን በከፍተኛ ሁኔታ ማስፋፋት ነው።
ይህ አጋርነት በዘርፉ የተሰማሩ የግል ድርጅቶችን ለመደገፍና የተጀመረውን የልማት ስራ ለማጠናከር ትልቅ እገዛ እንዳለው ከንቲባዋ ገልጸዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለማርያም ሳሊም እና ለቴክኒካል ቡድናቸው በራሳቸውና በከተማው ህዝብ ስም ከልብ የመነጨ ምስጋና አቅርበዋል።
