ሜታ ከግማሽ ቢሊዮን ዶላር በላይ ተቀጣ

Date:

ሜታ የተሰኘው ማኅበራዊ ሚዲያ ኩባንያ ህጻናትን ከኦንላይን አደጋዎች መጠበቅ አልቻለም እና «በሕዝብ ላይ ስጋት» ሆኗል በሚል በኒው ሜክሲኮ ግዛት ፍርድ ቤት ከግማሽ ቢሊዮን ዶላር በላይ (በአጠቃላይ 567 ሚሊዮን ዶላር) የገንዘብ ቅጣት ተላለፈበት።

የኒው ሜክሲኮ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ራኦል ቶሬዝ በጎርጎርሳዊው 2023 ባቀረቡት ክስ፤ የሜታ አልጎሪዝም አዋቂዎችን ወደ ታዳጊዎች ይዘቶች እንዲመሩ እንደሚያደርግ እና ኩባንያው በወጣቶች ላይ ስላለው አደጋ በውስጥ ጥናት ያወቃቸውን መረጃዎች ደብቋል የሚል የተጠቃለለ ክስ መቅረቡ ታውቋል።

ከተላለፈው አጠቃላይ የገንዘብ ቅጣት ውስጥ ሦስት አራተኛው በአምስት ዓመታት ውስጥ ተከፍሎ ለአእምሮ ጤና ህክምና የሚውል ሲሆን፤ ቀሪው ገንዘብ ደግሞ ለግንዛቤ ማስጨበጫ እና መከላከያ መርሃግብሮች ይከፋፈላል ተብሏል።

ሜታ በውሳኔው እንደማይስማማና ይግባኝ እንደሚል ቢገልጽም፣ ፍርድ ቤቱ ግን ህጻናትን ለጥቃት በመዳረጉ ጥፋተኛ ሆኖ ማግኘቱን አስታውቋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኢትዮጵያዊዉ የመጀመሪያው የአይን ሐኪም ዶክተር ጳውሎስ አረፉ

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የዓይን ሐኪም እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዓይን...

ኢትዮጵያውያን ታዳጊዎች በዓለም አቀፍ የሮቦቲክስ ውድድር 3ኛ ወጡ

በካናዳ በተካሄደው ዓለም አቀፍ የሮቦቲክስ ውድድር ላይ የተሳተፉት የኢትዮ...

ሁቲዎች የሳዑዲ የነዳጅ ማጣሪያ ላይ ጥቃት መፈፀማቸውን ገለጹ

የኢራን አጋር የሆኑት ሁቲዎች የሳዑዲ አራምኮ ጃዛን ነዳጅ ማጣሪያን...

በዓለም ከ20 ዓመት በታች ሻምፒዮና ኢትዮጵያ 2ኛ የወርቅ ሜዳሊያ አገኝች

በሴቶች 3 ሺህ ሜትር የተወዳደሩት  ዮርዳኖስ ጽጋብ እና ሽቶ...