አቶ ግርማ ዋቄ አዳዲስ እጩዎችን በመስከረም ወር ለቦርድ እንደሚያቀርቡ አስታወቁ

Date:

የኡጋንዳ አየር መንገድ ጊዜያዊ ዋና ስራ አስፈፃሚ እና አማካሪ አቶ ግርማ ዋቄ ቋሚ ዋና ስራ አስፈፃሚ ለመሾም የሚያስችላቸውን እጩዎች ዝርዝር በመጪው መስከረም ወር ለዳይሬክተሮች ቦርድ እንደሚያቀርቡ ተናግረዋል።

አቶ ግርማ የተወሰኑ ስሞችን እና የትምህርት ዝግጅት መግለጫዎችን (ሲቪ) ማጋራታቸውን ገልጸው፣ የውይይት መድረኩ በመስከረም ወር እንደሚካሄድ አስታውቀዋል።

ታዋቂው የኢትዮጵያ አቪዬሽን ባለሙያ ይህንን አስተያየት የሰጡት አየር መንገዱን የማረጋጋት ስራዎችን ሂደት እና አዲስ ቋሚ ዋና ስራ አስፈፃሚ የመምረጥ ሂደትን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ ላይ ነው።

አቶ ግርማ የቀድሞዋን ዋና ስራ አስፈፃሚ ጄኒፈር ባሙቱራኪ መልቀቅ ተከትሎ፣ በካቢኔ ውሳኔ በፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ አማካኝነት የካቲት 2026 ላይ ጊዜያዊ ዋና ስራ አስፈፃሚ እና አማካሪ ሆኖ እንዲያገለግሉ ተሹመዋል። የፕሬዚዳንቱ አስተዳደር በአየር መንገዱ ላይ የሚታዩትን የአመራር ድክመቶች ለማስተካከል አቶ ግርማ የዕለት ተዕለት ስራዎችን እንዲቆጣጠሩ አዟል።

የአቶ ግርማ ዋና ትኩረት የቆሙ አውሮፕላኖችን ወደ አገልግሎት መመለስ፣ የጥገና ክፍተቶችን ማስተካከል እና አጠቃላይ የሪፎርም ስራዎችን ማከናወን በመሆኑ የሹመቱ ሂደት ትንሽ ጊዜ ወስዷል።

ምንም እንኳን አስቸጋሪ ጊዜ አሳላፊ ቢሆንም፣ የሀገሪቱ የትራፊክ ፍሰትና የሰለጠነ የሰው ሃይል ለአየር መንገዱ እድገት ትልቅ ተስፋ የሚሰጥ መሆኑን አቶ ግርማ አፅንኦት ሰጥተው ገልጸዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የታሰሩ የፖለቲካ ታጋዮች እንዲፈቱ ተጠየቀ

ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት መንግሥት በጠባብ ቀዳዳ የምታየውን የፖለቲካ ምኅዳር...