ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የኮሎምቢያ አምባሳደር ጋር ተወያዩ

Date:


የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የኮሎምቢያ አምባሳደር ዬሶን አርካዲዮ ሜኔስ ኮፕቴን በጽ/ ቤታቸው በመቀበል ውይይት አድርገዋል።

በውይይታቸውም ሁለቱ አገራት በትምህርቱ ዘርፍ በትብብር መስራት የሚችሉባቸውን ጉዳዮች አንስተው ተወያይተዋል።

በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የኮሎምቢያ አምባሳደር በጽ/ቤታቸው ተቀብለው በማነጋገራቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸው በትምህርቱ ዘርፍ በትብብር ለመስራት የሚያስችሉ ጉዳዮችን ለአምባሳደሩ አንስተውላቸዋል።

በተለይም በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ በተማሪዎች ነጻ የትምህርት እድል፣ በሙዚቃና ባህል ልውውጥ እንዲሁም በሌሎች ጉዳዮች በትብብር መስራት እንደሚቻልም አብራርተዋል።

በኢትዮጵያ የኮሎምቢያ አምባሳደር ዬሶን አርካዲዮ ሜኔስ ኮፕቴ በበኩላቸው ኮሎምቢያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ኤምባሲዋን በአዲስ አበባ መክፈቷን ገልጸው በትምህርቱ ዘርፍም ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር መስራት እንደምትፈልግ ተናግረዋል።

አክለውም በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ነጻ የትምህርት እድልና የባለሙያ ልውውጥ፣ በከፍተኛ ትምህርት የሰላም ግንባታ እንዲሁም በሙዚቃና ባህል ልምድ ልውውጥ በማድረግ ረገድ በትብብር መስራት እንደሚፈልጉም አንስተዋል።

ሁለቱ አካላት በቀጣይ በሚኖራቸው ግንኙነቶች በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረጉ የጋራ ትብብሮችን አጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...