ደቡብ ሱዳን በሁለት ዓመታት ልዩነት ሦስተኛ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ሾመች

Date:

ደቡብ ሱዳን በሁለት ዓመታት ልዩነት ሦስተኛ የውጪ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር ተሾመላት። የሀገሪቱ ፕሬዝደንት ሳልቫ ኪር ሚያርዲት አዲስ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር የሾሙት ከተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝደንት ሪየክ ማቻር የገቡበት የፖለቲካ ውዝግብ ሀገሪቱን ወደ የርስ በርስ ጦርነት ሊከታት ይችላል የሚል ሥጋት ባየለበት ወቅት ነው።

አዲሱ የደቡብ ሱዳን የውጪ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር አምባሳደር መንደይ ሰማያ ኩምባ ትላንት አርብ ፕሬዝደንቱ በተገኙበት ቃለ-መሐላ ፈጽመዋል። አምባሳደር መንደይ የደቡብ ሱዳንን የውጪ ጉዳይ ፖሊሲ እንዲያራምዱ እና የሀገሪቱን ገጽታ እንዲያሻሽሉ ትዕዛዝ ተሰጥቷቸዋል።
አምባሳደር መንደይ ከሹመታቸው በፊት በምክትል የውጪ ጉዳይ ሚኒስትርነት ሲሰሩ ነበር። የቀድሞው የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ረመዳን አብደላ ጎክ ከኃላፊነታቸው ለምን እንደተሻሩ የተባለ ነገር የለም።

ረመዳን አብደላ ጎክ በውጪ ጉዳይ ሚኒስትርነት ደቡብ ሱዳንን የመሩት ለአንድ ዓመት ገደማ ብቻ ነው። ረመዳን አብደላ በሚያዝያ 2016 በውጪ ጉዳይ ሚኒስትርነት የተሾሙት ዶክተር ጄምስ ፒቲያ ሞርጋን ከኃላፊነቱ ከተባረሩ በኋላ ነበር።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...