የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከ59 ቢሊየን ብር በላይ እንደሚያስፈልገው ገለጸ

Date:

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የተሻለ የትምህርት ተቋም ለመሆን በቀጣይ አምስት ዓመታት ውስጥ 59 ቢሊየን ብር እንደሚያስፈልገው የዩኒቨርሲቲው ተጠባባቂ ፕሬዝደንት ሳሙኤል ክፍሌ አስታወቁ።

ዩኒቨርሲቲው በአሁኑ ወቅት በዓመት ከአራት ቢሊየን ብር የመንግስት በጀት እንዲሁም ከአንድ ቢሊየን ብር የራሱ ገቢ ያገኛል።

ሆኖም ፕሬዝደንቱ ይህ በቂ እንዳልሆነና ዩኒቨርሲቲው የትምህርት ጥራቱን ለማሻሻል፣ ምርምሮችን ለማስፋፋትና ለተማሪዎች ምቹ የሆነ የትምህርት ከባቢ ለመፍጠር በዓመት ከ11 ቢሊየን ብር በላይ እንደሚያስፈልገው ተናግረዋል።

የገንዘብ እጥረት ዩኒቨርሲቲው እነዚህን ግቦች ለማሳካት በሚያደርገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየሆነ መሆኑንም ፕሬዝደንት ሳሙኤል ክፍሌ ገልጸዋል።

ቅዳሜገበያ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በመንገድ የትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ህይወት አለፈ

አደጋው የደረሰው ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ/ም ከጠዋቱ...

ከ12ኛ ክፍል ተፈታኞች  565 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ አላሳለፉም

በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በተመዘገበው ውጤት...

የአማርኛ ቋንቋ እውነተኛ ምንጭ ቤተ መንግሥት ሳይሆን ሕዝብና ሠራዊት ነው

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአማርኛ ቋንቋ ማበልጸጊያ ተቋም አዘጋጅነት ከስድስት...