የሰደድ እሳቱ የተነሳው በእየሩሳሌም እና በዋና ከተማዋ ቴልአቪቭ አቅራቢያ ሲሆን እሳቱን ለመቆጣጠር የእስራኤል ባለስልጣናት ኤሊኮፍተሮችን እና የእሳት አደጋ መኪኖችን ወደ ስፍራው በመላክ እሳቱን ለመቆጣጠር ርብርብ እያደረጉ እንደሚገኙ ተገልጿል። የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስቴር ቢኒያሚን ኔታንያሁ በሀገሪቱ የተነሳውን እሳት ለመቆጣጠር ከባድ መሆኑን ገልጸው የሰደድ እሳቱ የሚባባስ ከሆነ እስራኤል ለአጋር ሀገራት እርዳታን ትጠይቃለች ሲሉ ገልጸዋል።
በእስራኤል ከተሞች በከባድ ሙቀት ምክንያት ከፍተኛ የሰደድ እሳት መነሳቱ ተነግሯል
Date:
