የኤሌትሪክ ተሽከርካሪዎች አምራች እና አከፋፋይ ዶዳይ ማኑፋክቸሪንግ  ከአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ  ጋር አብሬ መስራት ጀመርኩ አለ

Date:


ዶዳይ የሐገሪቱን የኤሌትሪክ ትራንስፖርት አጀንዳ ለመደገፍ ባለኝ ቁርጠኝነት 40  የኤሌክትሪክ   ሞተሮች  ለአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ሰጥቻለሁ ብሏል።

የተበረከቱት ኤሌክትሪክ -ሞተር ሳይክሎች ከዶዳይ ዘመናዊ የባትሪ መለዋወጫ አውታር ጋር ሙሉ ለሙሉ የተገናኙ ሲሆኑ  ከዶዳይ ስማርት ኔትወርክ ጋር የተገናኙ በመሆናቸው፤ አሸክርካሪዎች በስልካቸው ክፍያ እንዲከፍሉ እና ሃይል ያለቀበትን ባትሪያቸውን በ5 ደቂቃ ወዲያውኑ ሙሉ በሙሉ ቻርጅ ባረገ ባትሪ እንዲቀበሉ ያስችላቸዋል ተብሏል ።

ኩባንያው ከአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ጋር ያደረገው ስትራቴጂካዊ ትስስር የከተማ ትራንስፖርትን ለማሳደግ፣ የኤሌትሪክ ተሽከርካሪ ዘላቂነት ለማስተዋወቅ እና ለአዲስ አበባ ነዋሪዎች አዲስ የስራ እድሎችን ለመፍጠር ያለመ ነው መሆኑ ተጠቅሷል።

የዶዳይ ማኑፋክቸሪንግ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዩማ ሳሳኪ ” ከአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ እና ከወሳኝ የከተማ ተቋማት ጋር በመተባበር ስራ በመጀመራችን ደስታ ይሰማናል” ሲሉ መናገራቸው ተሰምቷል ።

የጃፓኑ ዶዳይ ኩባንያ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች አምራችና አከፋፋይ  ሲሆን አዳዲስ እና ዘላቂ የትራንስፖርት መፍትሄዎችን ለማቅረብ ቁርጠኛ ነኝ ብሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...