በአምስተኛው እና በመጨረሻ የግንባታ ምዕራፍ ላይ የሚገኘው ፕሮጀክት ከ13 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ያለማል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተገልጿል።
በሌላ በኩል በአካባቢው የሚገኙ ኢንቨስተሮች እና አርሶአደሮች በ430 ሄክታር መሬት ላይ ሙዝ፣ አቮካዶና ፓፓያ እያመረቱ እንደሆነና ወደ ውጭ ለመላክ እንቅስቃሴ መጀመራቸው ተገልጿል።
አልሚዎቹ ለእርሻ ማስፋፊያ 700 ሄክታር መሬት መውሰዳቸውንና በቀጣይ የእርሻ ምርት ማቀነባበሪያ ላይ ለመሥራት ማቀዳቸውን የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
በጊዳቦ ግድብ ግንባታ በጠቅላላው 304 ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል ተፈጥሯል።
