የጋዛ የእርዳታ ጣቢያዎች ተዘጉ

Date:

የእስራዔል ጦር በጋዛ የእርዳታማሰራጫ ጣቢያዎችን መዘጋቱን አስታወቀ።

ጦሩ ባወጣው መግለጫ ወደ እርዳታ ጣቢያዎች የሚያመሩ መንገዶች እንደ “ጦርነት ቀጠና” ይቆጠራሉ ሲል አስጠንቅቋል።

የጋዛ ሰብአዊ ፋውንዴሽን ጣቢያዎቹ “ለማዘመን እና አደረጃጀትና አፈጻጸማቸውንለማሻሻል” መዘጋታቸውን አስታውቋል።

በትናንትናው ዕለት የእስራዔል ጦር በእርዳታ ማደያ ጣቢያ አቅራቢያ በከፈተው ተኩስ 27 ሰዎች መገደላቸውን የጋዛ ጤና ሚኒስቴር መግለጹ ይታወሳል።

በወቅቱ የእስራዔል ጦር በእርዳታ ማደያ ጣቢያው አቅራቢያ ተጠርጣሪ ግለሰቦችወደ እነርሱ እያመሩ በነበረበት ወቅት ተኩስ መክፈታቸውን ነው የገለጸው።

የተመድ የህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) በበኩሉ የእርዳታ ማሰራጫ ጣቢያዎች
መዘጋትን ኮንኗል።

ዩኒሴፍ አሁን እየቀረበ ያለው እርዳታ እጅግ አነስተኛ ሆኖ እያለ ይህን ውሳኔመወሰን አላስፈላጊና አረመኔያዊነት ነው ብሏል።

በጋዛ የዩኒሴፍ ቃል አቀባይ ጀምስ ኤልደር በርካታ ታዳጊ ህጻናት ከ15 እስከ
20 ኪሎ ሜትር እርዳታ ፍለጋ በእግራቸው ይጓዛሉ ብለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...