የአረፋ በዓል ስናከብር ለተቸገሩ ወገኖች በማካፈል ሊሆን ይገባል

Date:


ሕዝበ ሙስሊሙ የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓልን ሲያከብር የተቸገሩ ወገኖችን በማሰብና ያለውን በማካፈል መሆን እንዳለበት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትአስታወቀ፡፡

ምክር ቤቱ ለመላው የእስልምና ዕምነት ተከታዮች እንኳን ለ1 ሺህ 446ኛው ዓመተ ሂጅራ የኢድ አል አድሃ አረፋ በዓል አደረሳችሁ ሲል መልዕክት አስተላልፏል።

ኢድ አል አድሃ የመተሳሰብ በዓል ነው ያሉት የምክር ቤቱ ፕሬዚዳንት ሼይኽ ሐጂ ኢብራሒም ቱፋ፤ ህዝበ ሙስሊሙ በዓሉን ሲያከብር የተቸገሩ ወገኖቹን በማሰብና ያለውን በማካፈል ሊሆን እንደሚገባ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስገንዝበዋል።

በእስልምና አስተምሮ መሰረት የአረፋ ቀን ዋጋዋ ትልቅ በመሆኗ መላው ህዝበ ሙስሊም በጾምና በዱዓ (በጸሎት) እንዲያሳልፉ ሼይኽ ሐጂ ኢብራሒም መልክታቸውን አስተላልፈዋል።

እርድ ማከናወን ለማይችሉ አቅመ ደካሞችንና አሳዳጊ የሌላቸውን ህጻናት እንዲሁም ድጋፍ የሚፈልጉ ወገኖችን ሁሉ አቅም በፈቀደ መጠን በመደገፍ እንዲያከብር ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ኢትዮጵያ የተለያየ እምነት ተከታይ ለበርካታ ዘመናት ተዋዶና ተከባብሮ የኖረባት ሀገር እንደመሆኗ ምዕመኑ ከሌሎች እምነት ተከታዮች ጋር አንድነቱንና ወንድማማችነቱን ይበልጥ በማጠናከር በዓሉን ማሳለፍ እንዳለበት ጥሪ አቅርበዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...