ለሰባት ቀናት ምህላ ታወጀ

Date:

በሰሜን ወሎ መንበረ ጵጵስና ሀገረ ስብከት በተለይ በቆላማ ወረዳዎች ክረምቱ ወቅቱን ጠብቆ ባለመግባቱና የዝናብ እጥረት በመከሰቱ ጸሎተ ምኅላ ታውጇል።

ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ኹሉም ገዳማት፣ አድባራትና አጥቢያ አብያተክርስቲያን ከዛሬ ሐምሌ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለ7 ቀናት የሚቆይ ምኅላ አውጀዋል።

ኹሉም ሕዝበ ክርስቲያን በየአብያተ ክርስቲያናቱ ዘወትር ጠዋት በመገኘት በተሰበረ ልብ ወደ እግዚአብሔር እንድጸልይ ብፁዕነታቸው ትናንት ሐምሌ 19 ቀን 2017 ዓ.ም አባታዊ መልእክት አስተላልፈዋል። 

ትናንት አዳሩን በወልዲያ መጠነኛ ዝናብ ቢዘንብም በቆላማው ቀበሌዎች፣ በቆቦ፣በአላማጣ እንዲሁም በራያ አዘቦ እስካሁን ዝናብ እንዳልዘነበ ተሰምቷል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...