ምርጫ ቦርድ ሁለተኛ ዙር የምርጫ ጣቢያዎችን   በዲጂታል ሲስተም መመዝገብ  ጀመረ

Date:

የኢትዯጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እንደ አዲስ ከተቋቋመበት 2011 ዓ.ም. አንሥቶ አንድ ሀገራዊ ምርጫ እና ሦስት ሕዝብ ውሣኔዎችን ማስፈጸሙ ይታወቃል።  ቦርዱ በቀጣይም የ7ኛውን ዙር ሀገራዊ ምርጫ ለማከናወን የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል። 

ስለሆነም ቦርዱ በቀጣይ የሚያከናውናቸው ምርጫዎች ከዚህ በፊት ከተካሄዱት ምርጫዎች በአፈጻጸም ቀልጣፋና ጊዜው የሚጠይቀውን ዘመናዊነት የተከተሉ ለማድረግ፤  የምርጫ ጣቢያ እና የምርጫ ክልል ጽ/ቤቶች በተለያዩ ባለድርሻ አካላት በርቀታቸው፣ በመልካ-ምድራዊ አቀማጣቸው የታወቁ እና የተለዩ እንዲሁም ለመራጩ  ሕዝብ ምቹና ተደራሽ እንዲሆኑ፣

በተጨማሪም ሕግን መሠረት አድርገው የተቋቋሙ መሆናቸዉን የማረጋገጥ እና መረጃዎች በተሟላ መንገድ የማደራጀት ሥራ አስፈላጊ በመሆኑ፤ ምርጫ ጣቢያዎቹ የሚገኙበት ትክክለኛ ቦታዎች የGIS ቴክኖሎጂን በመጠቀም በ‘’XY Coordinate’’ የመለየት እና የመመዝገብ ሥራ እያከናወነ ይገኛል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ምግባረ-መልካሙ ኢትዮጵያዊ

ስለሺ መንገሻ - ከ1934 እስከ 2018 ዓ.ም ሠሎሞን ለማ ገመቹ. ግዮን...

ትራምፕ ለኔታንያሁ ማስጠንቀቂያ ሰጡ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ...

ኤምባሲዎችና የውጭ ባለሀብቶች በ«ፍራንኮ-ቫሉታ» ነዳጅ እንዲያስገቡ ተፈቀደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ኤምባሲዎች፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እና የውጭ...

የሪል ስቴት ኢንቨስትመንት ከዓመታዊ የትርፍ 90 በመቶውን እንዲያከፋፍሉ ሊደረግ ነው

የሪል ስቴት ኢንቨስትመንት ተብለው የሚቋቋሙ ፈንዶች ከዓመት ትርፋቸው ቢያንስ...