ሞስኮና ቤጂንግ በሆርሙዝ ወሽመጥ ቀዉስ ሳቢያ ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸዉ ጠብቋል

Date:

በትራምፕ የውጭ ፖሊሲ እና በሆርሙዝ ወሽመጥ ቀውስ ሳቢያ ይበልጥ እየተቀራረበ የመጣው የሞስኮ እና የቤጂንግ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ጠብቋል ነዉ የተባለዉ፡፡

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቤጂንግን ጎብኝተው በወጡ በጥቂት ቀናት ውስጥ፣ ቻይና የሩሲያውን ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲንን በማስተናገድ ላይ ትገኛለች።

የትራምፕ የውጭ ፖሊሲ ሊገመት አለመቻል ሞስኮ እና ቤጂንግን ይበልጥ እያቀራረባቸው መሆኑን ተንታኞች ይገልጻሉ።

ይህ የሁለቱ አገራት ጥልቅ አጋርነት የመጣው በዩክሬን ጦርነት እና በኢራን ውጥረት ሳቢያ በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በትራንስፖርት መስተጓጎል በተፈጠረው ቀውስ ነው።

ስትራቴጂካዊው የውሃ መስመር አደጋ ላይ በመውደቁ ቻይና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ለማግኘት ይበልጥ ወደ ሩሲያ ፊቷን አዙራለች።

ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ ሁለቱንም መሪዎች በአንድ ሳምንት ልዩነት ማስተናገዳቸው በአጋጣሚ የተከሰተ እንዳልሆነ የሚናገሩት ተንታኞች፤ ይህም ቤጂንግ በተከፋፈለው የዓለም ሥርዓት ውስጥ ራሷን እንደ ታማኝና ተደማጭነት ያላት ተዋናይ አድርጋ ለማቅረብ የምታደርገውን ስትራቴጂካዊ ጥረት ያሳያል ብለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ቱርክ ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ የእስር ማዘዣ አወጣች

ቱርክ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ ዓለም አቀፍ...

በመቀለ የሚካሄደው የአሸንዳ በዓል የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ተሰረዘ

በትግራይ በርካታ ታዳሚ በሚገኝበት በየዓመቱ የሚከበረው የአሸንዳ ባህላዊ በዓል...

የኢትዮጵያ ፖስታ 3 ሺሕ የሚጠጉ ቅርንጫፎቹን ወደ ባንክ ኤጀንትነት ለመቀየር እንቅስቃሴ ጀመረ

የኢትዮጵያ ፖስታ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ 3 ሺሕ በሚጠጉ ቅርንጫፎቹ...

«ግብጽ ዛቻውን አቁማ ወደ ድርድር ትግባ!»

ታዋቂው የአፍሪካ ፖለቲካ ተንታኝ ዶ/ር ዴቪድ ማትሳንጋ ግብጽ በኢትዮጵያ...