ሩሲያ ለኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ድጋፍ ታደርጋለች

Date:

የሩሲያ የኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር ማክሲም ሬሼትኒኮቭ ከኢትዮጵያ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ ጋር የበይነመረብ ውይይት ባደረጉበት ወቅት የሞስኮን ድጋፍ አረጋግጠዋል፡፡

“የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት በውይይቱ ተነስቷል። የሩሲያ ወገን የኢትዮጵያን እቅዶች ሙሉ በሙሉ እንደሚደግፍና የቴክኒክና የማማከር ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ገልጿል” ሲል የሩሲያ የኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ከውይይቱ በኋላ ባወጣው መግለጫ ማስታወቁን ስፑትኒክ ዘግቧል፡፡

ሬሼትኒኮቭ የሩሲያና ኢትዮጵያ የንግድ ልውውጥ መጠን እያደገ መሄዱንም ጠቁመዋል። እ.ኤ.አ በ2025 የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ2.2 ጊዜ ጨምሮ 191.2 ሚሊየን ዶላር ደርሷል ብለዋል።

ሩሲያ በዋናነት ከኢትዮጵያ የቡና ምርት እያስገባች እንደሆነም ገልጸዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...