በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ አርሰናል እና ባርሴሎና ለፍጻሜ ደረሱ

Date:



በሴቶች የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ግማሽ ፍጻሜ የመልስ ጨዋታ አርሰናል ከሜዳው ውጭ ወደ ፈረንሳይ ተጉዞ ሊዮንን 4 ለ 1 አሸንፏል።

በሊዮን በተደረገው  ጨዋታ ማሪዮና ካልደንቲ ፣ አሊሲያ ሩቶ ፣  ኬትሊን ፎርድ እና ኢንድለር በራሷ መረብ ላይ የአርሰናልን ግቦች አስቆጥረዋል።

ዱሞናይ የሊዮንን አንድ ግብ ያስቆጠረች ተጫዋች ሆናለች።

በመጀመርያው ጨዋታ በሜዳው 2 ለ 1 ተሸንፎ የነበረው አርሰናል ውጤቱን ቀልብሶ በድምር ውጤት 5 ለ 3 በማሸነፍ  ከ18 አመት በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ የፍጻሜ ተፋላሚ መሆኑን አረጋግጧል።

በሌላ የግማሽ ፍጻሜ የመልስ ጨዋታ ባርሴሎና ቼልሲን 4 ለ1 አሸንፏል።

በመጀመርያው ጨዋታም በተመሳሳይ 4 ለ 1 ያሸነፈው ባርሴሎና በድምር ውጤት 8 ለ 2 በማሸነፍ ለዋንጫ ጨዋታ ደርሷል።

በፍጻሜው አርሰናል ከባርሴሎና በሊዝበን የሚገናኙም ይሆናል።

በአንተነህ ሲሳይ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...