በየመን  ሕገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ላይ ዘመቻ መጀመሯ ተሰምቷል

Date:

በድርጊቱ በሚሳተፉ ላይ ጥብቅ እርምጃ ይወሰዳል ተብሏል።

በቅርቡ በደቡብ አቢያን ግዛት ጀልባ ሰጥሞ ከ90 በላይ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች መሞታቸውን ተከትሎ፤ አፍሪካውያን ስደተኞችን በሀገሪቱ በኩል የሚያንቀሳቅሱ ሕገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ላይ ዘመቻ መጀመራቸውን የየመን ባለሥልጣናት ከትላንት በስቲያ ረቡዕ  አስታውቀዋል፡፡

የአቢያን ግዛት ፖሊስ ባወጣው መግለጫ፤ “የአፍሪካ ዜግነት ያላቸውን ፍልሰተኞችና ስደተኞችን በማጓጓዝ ወይም በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ ተሳትፎ የተገኘ የትኛውም አካል ላይ ጥብቅ እርምጃ ይወሰዳል” ብሏል፡፡

በአዲሱ እርምጃ መሠረት፤ የፀጥታ ኃይሎች በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር አገልግሎት ላይ የሚውሉ ተሽከርካሪዎች፣ ጀልባዎችና ሌሎች የመጓጓዣ ዘዴዎች እንደሚወረሱ ተጠቁሟል።
መረጃው የስፑትኒክ ኢትዮጵያ ነው።፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...