በድርጊቱ በሚሳተፉ ላይ ጥብቅ እርምጃ ይወሰዳል ተብሏል።
በቅርቡ በደቡብ አቢያን ግዛት ጀልባ ሰጥሞ ከ90 በላይ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች መሞታቸውን ተከትሎ፤ አፍሪካውያን ስደተኞችን በሀገሪቱ በኩል የሚያንቀሳቅሱ ሕገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ላይ ዘመቻ መጀመራቸውን የየመን ባለሥልጣናት ከትላንት በስቲያ ረቡዕ አስታውቀዋል፡፡
የአቢያን ግዛት ፖሊስ ባወጣው መግለጫ፤ “የአፍሪካ ዜግነት ያላቸውን ፍልሰተኞችና ስደተኞችን በማጓጓዝ ወይም በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ ተሳትፎ የተገኘ የትኛውም አካል ላይ ጥብቅ እርምጃ ይወሰዳል” ብሏል፡፡
በአዲሱ እርምጃ መሠረት፤ የፀጥታ ኃይሎች በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር አገልግሎት ላይ የሚውሉ ተሽከርካሪዎች፣ ጀልባዎችና ሌሎች የመጓጓዣ ዘዴዎች እንደሚወረሱ ተጠቁሟል።
መረጃው የስፑትኒክ ኢትዮጵያ ነው።፡
