ዛሬ የቱርኩ ፕሬዝደንት ሬሴፕ ጣይብ ኤርዶጋን እና የሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላዲሚር ፑቲን በስልክ ተነጋገረዋል። ሁለቱ መሪዎች በዩክሬን ጦርነት ዙሪያ ስላሉት ሁኔታዎች ተወያይተዋል።
የቱርክ ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት ባወጣው መግለጫ መሠረት፣ ሬሴፕ ጣይብ ኤርዶጋን ለሩሲያው አቻቸው “የሰላም ሂደቱን ሁኔታ በቅርበት እየተከታተለ መሆኑን፣ ቱርክ ከጦርነቱ መጀመሪያ ጀምሮ ፍትሃዊ ሰላም ለማምጣት ቅን ጥረት ስታደርግ እንደቆየች እና ሁሉም አካላት በሚሳተፉበት ዘላቂ ሰላም ለመመስረት ያለመ አቋምን እንደምትደግፍ” ገልጸዋል።
የሩሲያው ፕሬዝደንት በኢስታንቡል የተካሄደውን የሩሲያ እና የዩክሬን ልዑካን ስብሰባ በመጥቀስ፣ ቱርክ የሰላም ንግግሩን በማስተናገዷ እና ለሚያደርገው ጥረት ጣይብ ኤርዶጋንን አመስግነዋል።
