በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በተከሰተ የእንስሳት በሽታ የሞቱ ከብቶች ብዛት 1,400 ደረሰ

Date:

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በሚገኙ አራት ዞኖች ካለፈው ሳምንት መጨረሻ ጀምሮ በተከሰተ የእንስሳት በሽታ ወረርሽኝ፤ ከ1,400 በላይ ከብቶች መሞታቸውን የአካባቢው የስራ ኃላፊዎች ተናገሩ። በክልሉ የሚገኙ 6,500 የሚሆኑ ከብቶች የበሽታው ምልክት እንደታየባቸው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ገልጿል።

ከጋሞ ዞን ወደ ጎፋ፣ ደቡብ ኦሞ እና አሌ ዞኖች የተዛመተው የእንስሳት በሽታ ወረርሽኝ፤ በዋናነት የሚያጠቃው በሬዎችን እና ላሞችን ነው። በወረርሽኙ የተጠቁ ከብቶች፤ ከፍተኛ የሰውነት ሙቀት፣ የመተንፈሻ አካላት ጭንቀት እና ሳል፣ ከአፍንጫቸው ውሃ የሚመስል ፈሳሽ መውጣት እና የምግብ ፍላጎት መቀነስ ምልክቶች ይታዩባቸዋል።

ምንነቱ እስካሁን በምርመራ ያልታወቀው ይህ የእንስሳት በሽታ፤ በከብቶች ጭንቅላት እና ትከሻቸው አካባቢ እብጥት ያስከትላል። “የከብቶችን አቅም በማዳከም በፍጥነት እንደሚገድል” የሚነገርለት ይህ በሽታ ለመጀመሪያ ጊዜ በታየበት በጋሞ ዞን ጋርዳ ማርታ ወረዳ ብቻ 693 ከብቶች ባለፉት አምስት ቀናት ውስጥ መሞታቸውን የወረዳው ግብርና መምሪያ  ገልጿል።  

የጋርዳ ማርታ ወረዳ የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አዲሱ ሀሼ፤ በሽታው “በፍጥነት የሚዛመት” እንደሆነ አስረድተዋል።

የአካባቢው አርብቶ አደሮች ከአንድ ቦታ ወደ አንድ ቦታ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ምክንያት፤ በሽታው ወደ ጎፋ ዞን ተዛምቶ 216 ከብቶች መሞታቸውን የዞኑ የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ደግፌ ተናግረዋል።

@Ethiopianinsider

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር፤ ለወረራ የታለመ ማደናገሪያ? ሩሲያ ማስጠንቀቂያ ሰጠች!

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ውጥረትን ለመቀነስ...