ሱዳን እና ደቡብ ሱዳን ዜጎች ላይ ያተኮረ መጠነ-ሰፊ የዘፈቀደ እስራት እና ማባረር በግብፅ ባለስልጣናት እየተፈጸመ መሆኑን ሂውማን ራይትስ ዎች አስታወቀ።
ድርጅቱ ባወጣው አዲስ ሪፖርት መሠረት፣ በካይሮ የሚገኘው የተመድ የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን (UNHCR) ህጋዊ ሰነድ ያላቸው ስደተኞች ጭምር የነዋሪነት ፈቃዳቸው በማለቁ ምክንያት እየታሰሩና ወደየሀገራቸው እየተባረሩ ይገኛሉ።
የነዋሪነት ፈቃድ እድሳት ቀጠሮ በቢሮክራሲ መዘግየት ምክንያት እስከ 2020 ዓ.ም በመራዘሙ፣ ስደተኞቹ ያላንዳች ጥፋታቸው ለህግ ጥሰት ተጋልጠዋል።
ባለፉት ወራት በግብፅ የስደተኞች ቁጥር በሶስት እጥፍ ያደገ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ከ1.1 ሚሊዮን በላይ የተመዘገቡ ስደተኞች በሀገሪቱ ይገኛሉ።
ሂውማን ራይትስ ዎች ግብፅ በ2024 ያወጣችውን የአምስትነት ህግ ከአለም አቀፍ ስምምነቶች ጋር እንድታስማማ እና ያለፍርድ የሚደረገውን ማባረር እንድታቆም አሳስቧል።
ከፊደል ፖስት
