በ”ፊንቴክ” ኢንቨስትመንት በተጠረጠሩት ላይ ተጨማሪ ጊዜ ተፈቀደለት

Date:

ፖሊስ ተጨማሪ 14 ቀን ለምርመራ እንዲፈቀድለት ባለፈው አርብ በነበረው ችሎት  ጠይቆ ለውሳኔ ፍርድ ቤቱ ለዛሬ ቀጥሮ እንደነበር ይታወሳል፡፡

በ”ፊንቴክ”(Fintech) ኢንቨስትመንት ሽፋን በተፈጸመ የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮችን ጉዳይ ፖሊስ በጠየቀው የተጨማሪ ጊዜ ላይ ለመወሰን የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዛሬ ሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ለፖሊስ የ7 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ፈቅዷል።

ባለፈው ሚያዚያ 9 2018 ዓ/ም በነበረው ችሎት ባለፉት ቀናት  ያከናወናቸውን ተግባራት ለችሎቱ ያስረዳው ፖሊስ፣ ነገር ግን ከወንጀሉ ውስብስብነትና ስፋት አንፃር ቀሪ የምርመራ ስራዎችን ለማጠናቀቅ ተጨማሪ 14 ቀናት እንዲሰጠው ጠይቆ ነበር። 

በተቃራኒው የተጠርጣሪዎች ጠበቆች ደንበኞቻቸው በህዝብ ዘንድ የሚታወቁና ቋሚ መኖሪያ ያላቸው መሆኑን እና የራሳቸው መተዳደሪያ ስራ ያላቸውና አብዛኞቹም የጤና እክል ያለባቸው ናቸዉ በማለት የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸው ተከራክረዋል።

ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኙን ክርክር ካዳመጠ በኋላ፣ ውሳኔ ለመስጠት ለዛሬ ሚያዚያ 14 2018 ዓ/ም ቀጠሮ መስጠቱ ይታወሳል።

ዛሬ በነበረው ችሎት ፖሊስ የቀረውን ምርመራ አጠናቆ እንዲያቀርብ 7  ተጨማሪ ቀናት ፈቅዷል።

ተጠርጣሪዎቹ ለቀጣይ የችሎት ቀጠሮ ሚያዝያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም እንዲቀርቡ ፍርድ ቤቱ አዟል።

ሸገር 102.1

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...

ምንገድ ላይ

(በእውቀቱ ስዩም) በቀደም ከሆነ ቦታ ተነስቼ ወደ አልሆነ ቦታ ስራመድ...

ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነ ኢየሱስ በጡረታ ከኃላፊነታቸው ተሰናበቱ

የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያንና የአዲስ አበባ አገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ...