“ባለፉት 8 ዓመታት እንደ ላሚን ያማል ዓይነት ድንቅ ተጫዋች አይቼ አላውቅም” – ሲሞን ኢንዛ

Date:

“ባለፉት 8 ወይም 9 ዓመታት እንደ ላሚን ያማል ዓይነት ድንቅ ተጫዋች አይቼ አላውቅም” ሲሉ የኢንተር ሚላን አሠልጣኝ ሲሞን ኢንዛጊ ለተጫዋቹ አድናቆታቸውን ገልጸዋል።

ዛሬ ምሽት በተደረገው የሻምፒዮንስ ሊግ የግማሽ ፍፃሜ የመጀመሪያ ጨዋታ ባርሴሎና ኢንተር ሚላንን በሜዳው አስተናግዶ 3 አቻ ተለያይቷል።

በጨዋታው የባርሴሎናው አዳጊ ተጫዋች ላሚን ያማል ድንቅ ብቃቱን ያሳየ ሲሆን ጠንካራ የሚባለውን የኢንተር ሚላን የተከላካይ መስመር አታልሎ በማለፍ ለክለቡ አንድ ግብ አስቆጥሯል።

የ17 ዓመቱ ላሚን ያማል በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ታሪክ በግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ግብ ያስቆጠረ በዕድሜ ትንሹ ተጨዋች ሆኗል።

በዚህ ብቃቱ የተደነቁት የኢንተር ሚላኑ አሠልጠኛል ሲሞን ኢንዛጊ፣ “የእሱን እንቅስቃሴ ለመግባት ሁለት እና ሦስት ተጫዋችን መመደብ ነበብን” ሲሉ ከጨዋታው በኋላ ተናግረዋል።

“እንደ ላሚን ያማል ያሉ ባለድንቅ ተሰጥኦ ተጫዋቾች በየ50 ዓመቱ አንዴ የሚከሰቱ ናቸው” ሲሉም ነው አድናቆታቸውን የገለጹት።

የባርሴሎናው የአጥቂ መስመር ተጫዋች ላሚን ያማል በ17 ዓመቱ ዛሬ 100ኛ ጨዋታውን ማድረግ ችሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...