ትራምፕ የጄፍሪ ኤፕስቴይን ሰነዶች ይፋ እንዲሆኑ ጠየቁ

Date:

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሪፐብሊካን ፓርቲ አባላት ታዳጊዎችን በወሲብንግድ በማሰማራት የተፈረደበት ጄፍሪ ኤፕስቴይንን ሰነዶች ይፋ እንዲያደርጉ ጠየቁ።

ፕሬዚዳንቱ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ የተወካዮች ምክር ቤት አባላት “ምንም የምንደብቀው ነገር ስለሌለ”ሰነዱን ይፋ ማድረግ አለባቸው ብለዋል።

ትራምፕ ከዚህ ቀደም  ሰነዱ እንዳይለቀቅ ሲሟገቱ የቆዩ ሲሆን፥ አሁን ላይ ምክር ቤቱ በዚህ ሳምንት በጉዳዩ ላይ ስብሰባ አካሂዳለሁ ማለቱን ተከትሎ የሰነዱን ይፋ መሆን መደገፋቸውን ቢቢሲ አስነብቧል።

በስብሰባው ምክር ቤቱ የአሜሪካ ፍትህ ሚኒስቴር የግለሰቡን ሰነዶችይፋ እንዲያደርግ አስገዳጅ ድምፅ ይሰጣል ነው የተባለው።

ታዋቂ የቢዝነስና የፖለቲካ ሰዎች ከግለሰቡ ጋር ግንኙነት አላችሁበሚል በበርካታ መገናኛ ዘዴዎች ጭምጭምታዎች ሲደመጡ ቆይተዋል።

እስካሁን ለጭምጭምታዎች በቂ ማስረጃ ያልተገኘ ሲሆን፥ በታዳጊዎችየወሲብ ንግድ የሚጠረጠረው ኤፕስቴይንም በፈረንጆቹ 2019 በማረሚያ ቤትህይወቶ አልፎ መገኘቱን ዘገባው አስታውሷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኮሪያ ዘማቾች ያስመዘገቡት አኩሪ ታሪክ በዓለም ሲታወስ ይኖራል

75ኛ ዓመት የኮሪያ ዘማቾች መታሰቢያ በዓል አዲስ አበባ በሚገኘው...

አሜሪካ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ሳቢያ ኢራን 4.8 ቢሊዮን ዶላር አጣች

በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ በኦማን ባህረ ሰላጤ ላይ...

ኢሕአፓ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ማራዘሙን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ሚያዚያ 30 ቀን 2018...

እሁድ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ

መነሻውንና መድረሻውን መስቀል አደባባይ የሚያደረገው ዓለም አቀፉ የዛይድ የበጎ...