ቻይና አዲስ የሚወለዱ ህጻናትን እንደምታበረታታ ገለጸች

Date:

በቻይና ሆሆት ከተማ አስተዳደር ልጅ ለሚወልዱ እናቶች ለልጁ በየቀኑ አንድ ኩባያ ወተትና ለህጻኑ የእንክብካቤ ድጋፍ እንደሚደረግለት አስታውቀዋል፡፡

በመላው ቻይና በ20 ግዛቶች ይሄንን መሰል ድጋፍ ለሚወልዱ እናቶች እየቀረበ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን ፤እነዚህ ድጎማዎች ወጣት ጥንዶች ወደ ጋብቻ እንዲያመሩና ልጆችን እንዲወልዱ ለማበረታታት እንደሆነ የሃገሪቱ ሚዲያ ዢንዋ ዘግቧል፡፡

የቻይና ህዝብ የውልደት መጠን እጅግ ማሽቆልቆሉ መንግስትን ያሳሰበ ጉዳይ ሲሆን፤ አሁን ላይ ያለው የውልደት መጠን ከአንድ ሺ ሰዎች 6.77 በመቶ ብቻ እንደሆነ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡

በዚህም የቻይና መንግስት የስነ ህዝብ ፖሊሲ አውጪዎች ጥንዶች ልጆች እንዲወልዱ አዳዲስ መፍትሄዎች ላይ ጥናቶችን እያደረጉ ነው ተብሏል፡፡

በሌላ በኩል የ 2023 ጥናት እንደሚያሳየው በቻይና የአዛውንቶች ቁጥር 2መቶ97 ሚሊየን ደርሷል ፡፡

ቻይና 1.4 ቢሊየን የህዝብ ቁጥር ያላት ሲሆን፤ የዓለምን ህዝብ ቁጥር 17.4 በመቶ የሚሆነዉን ትሸፍናለች፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...