ንጉሥ አርማህ ቴአትር ከሩብ ምዕተ ዓመት በኋላ ወደ መድረክ ተመለሰ

Date:

ቴአትሩ በዶክተር ተሻለ አሰፋ ተዘጋጅቶ ቀደምትና አዳዲስ ተዋንያንን በመያዝ፣ በድርሰትና በዝግጅት ተሻሽሎ፣ በአዲስ መልክ ከእሑድ ሐምሌ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለዕይታ ሊበቃ እንደሆነ የቴአትሩ ጸሐፊ መልካሙ ዘርይሁን ገልጿል።

ሥድስት ወራት የልምምድ ጊዜ የፈጀው ይህ ታሪካዊ ቴአትር የተዋንያኑን አቅምና ብቃት በሚገባ መፈተን የቻለ እንደነበርም ሰምተናል።

የዛሬ 25 ዓመት በደራሲ መልካሙ ዘርይሁን ተፅፎ በማንያዘዋል እንደሻው የተዘጋጀው ንጉሥ አርማህ ቴአትር ተስፋዬ ገብረሃና እንደ ልዑል፣ ቅድስት ገ/ስላሴ እንደ ልዕልት በመሆን ተጫውተውታል።

ከ25 ዓመታት በኋላም ቴአትሩ ሲመለስ ሁለቱም ተዋንያን ንጉሥና ንግስት ሆነው እንደሚጫወቱ ከደራሲው ሰምተናል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...

ኧረ ፋታ ስጡን?!

መንግስት ግን" ምን ሁኑ ?" ሊለን ነው :: አጀንዳ...