አሃዱ ባንክ ከ2.1 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን ይፋ አደረገ

Date:

አሃዱ ባንክ ከ2.1 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በማስመዝገብን ያስታወቀ ሲሆን ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ1 ቢሊዮን ብር ጭማሪ ወይም የ90.9 በመቶ ዕድገት ማሳየቱን ገልጿል።

የባንኩ አጠቃላይ ትርፍ የእርጅና ቅናሽ እና ተያያዥ ወጪዎችን ጨምሮ፣ ለመጠባበቂያ ከተቀመጠው እና ከግብር በፊት 569 ሚሊዮን ብር ማትረፉን በሪፖርቱ ተመላክቷል።

ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከተገኘው ትርፍ በ450 ሚሊዮን ብር ብልጫ ያለው ሲሆን፣ የ278.1 በመቶ እድገት አስመዝግቧል።

የባንኩ ተቀማጭ ገንዘብ 7.8 ቢሊዮን ብር የደረሰ ሲሆን፣ ይህም ካለፈው የሒሳብ ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ68 በመቶ ዕድገት በማሳየቱና በውጭ ምንዛሪ ገቢ ረገድም ከ88 ሚሊዮን ዶላር በላይ መሰብሰብ መቻሉን አስረድተዋል።

የደንበኞች ቁጥር 1.1 ሚሊዮን መድረሱን የገለፀው ባንኩ አጠቃላይ ሀብቱ ከ10 ቢሊዮን ብር በላይ በማድረስ የ57 በመቶ ዕድገት ማስመዝገቡን አስታውቋልአስታውቋል።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር፤ ለወረራ የታለመ ማደናገሪያ? ሩሲያ ማስጠንቀቂያ ሰጠች!

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ውጥረትን ለመቀነስ...