አሜሪካ በስደተኞች ማዕከል ላይ በፈጸመችው ጥቃት 68 ሰዎች መገደላቸው ተሰማ

Date:

አሜሪካ በሁቲ ኃይሎች ቁጥጥር ሥር ባለው የሰሜን ምዕራብ የየመን ክፍል ውስጥ አፍሪካውያን ስደተኞች ተይዘው በሚገኙበት ማዕከል ላይ በፈጸመችው የአየር ጥቃት ቢያንስ 68 ሰዎች መገደላቸውን የታጣቂ ቡድኑ የቴሌቪዥን ጣቢያ ዘግቧል።

አል ማሲራህ የተባለው የሁቲ የቴሌቪዥን ጣቢያ እንዳለው ሳአዳ ግዛት ውስጥ በሚገኘው ማዕከል ላይ በተፈጸመው ጥቃት ከሞቱት በተጨማሪ አብዛኞቹ ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው 47 ሰዎች ቆስለዋል።

ጣቢያው በአንድ የወደመ ሕንጻ ፍርስራሽ ሥር የተቀበሩ የበርካታ ሰዎች አስከሬኖችን የሚያሳይ አሰቃቂ ምሥሎችን አሳይቷል።

ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ ከተለያዩ የአፍሪካ ቀንድ አገራት በርካታ ስደተኞች አደገኛውን የቀይ ባሕር መስመርን በሕገወጥ መንገድ በማቋረጥ ወደ የመን እንሚገቡ ይታወቃል።

ስደተኞቹ በጦርነት በምትታመሰው የመን በኩል በማቋረጥ የተሻለ ኑሮን ፍለጋ ወደ ሳዑዲ አረቢያ እና የባሕረ ሰላጤው አገራት ይጓዛሉ።

በዚህም በባሕር ላይ ጉዞ ከሚደርስባቸው አደጋ በተጨማሪ የመን ውስጥ በሚካሄደው ጦርነት ምክንያት ለጉዳት እንደሚጋለጡ ሱዘገብ ቆይቷል።

በአሜሪካ ጥቃት በስደተኞች ማቆያ ላይ ደረሰ ስለተባለው ጉዳት ከአሜሪካ ጦር ሠራዊት በኩል ወዲያውኑ የተሰጠ ምላሽ የለም።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...