አምዞን እና ዴልታ አየር መንገድ የሳተላይት ኢንተርኔት ስምምነት ተፈራረሙ

Date:

የአማዞን ኩባንያ የሳተላይት ኢንተርኔት ክፍል  ከዴልታ አየር መንገድ ጋር በ500 አውሮፕላኖች ላይ የዋይ ፋይ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ስምምነት መፈራረሙን አስታውቋል።

እ.ኤ.አ. በ2028 አገልግሎት መስጠት ይጀምራል ተብሎ የሚጠበቀው ይህ ስምምነት፣ አማዞን በዘርፉ ቀዳሚ ከሆነው የኢሎን ማስክ ‘ስታርሊንክ’ ጋር ያለውን ፉክክር ይበልጥ እንደሚያፋጥነው ተነግሯል።

ስታርሊንክ በአሁኑ ወቅት በሺዎች የሚቆጠሩ ሳተላይቶችን ወደ ህዋ በማምጠቅ የገበያ የበላይነቱን ቢይዝም፣ አማዞን ግን ከዴልታ በፊት ከጄት ብሉ ጋር በደረሰው ስምምነት መሰረት የገበያ ድርሻውን ለማስፋት በትኩረት እየሰራ ይገኛል።

ኩባንያው ከኤፕሪል 2025 ጀምሮ 214 ሳተላይቶችን ወደ ህዋ ያመጠቀ ሲሆን፣ በሚቀጥሉት 12 ወራት ውስጥ ከ20 በላይ መንኮራኩሮችን በመጠቀም የማምጠቅ አቅሙን እጥፍ ለማድረግ አቅዷል።

ዴልታ አየር መንገድ አማዞንን ለዚህ አገልግሎት የመረጠውም ቀደም ሲል ከአማዞን ዌብ ሰርቪስ ጋር ባለው ጠንካራ የክላዉድ ስሌት ሥራ ትብብር ምክንያት እንደሆነ ገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

‹‹ሀገር ጥለው የጠፉና ድርጅቶቻቸውን ለመዝጋት የተገደዱ አሉ››

አቶ አለማየሁ ከተማ(የኢትዮጵያ ሪልስቴት አልሚዎች ማኅበር ፕሬዝዳንት) ግዮን መጽሔት :-...

የሰላም ስምምነት ሳይፈጸም የንግድ መርከቦች ጉዞ እንደማይጀምሩ የነዳጅ ጫኝ ኩባንያ ኃላፊ ተናገሩ

የሲውዲን ነዳጅ አጓጓዥ ኩባንያ የሆነው ‘ስቴና በልክ’ ዋና ስራ...

የታሪካዊው ቁልቢ ገብርኤል የዕድሳት ጥሪ ፦ የ134 ሚሊዮን ብር ግዙፍ ፕሮጀክት

! ከተገነባ 64 ዓመታትን ያስቆጠረውና በየዓመቱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ምዕመናን የሚሳለሙት...

መርስክ የበርበራ ወደብ የጭነት አገልግሎቶችን ለጊዜው አቋረጠ

የዓለማችን ግዙፍ የመርከብ ድርጅት የሆነው መርስክ ፣ ወደ በርበራ...