አርሰናል ሁለት መንትዮች አስፈረመ !

Date:

የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል ኤድዊን እና ሆልጄር ኩንቴሮ የተባሉ ኢኳዶራዊ መንትዮች ማስፈረሙን በይፋ አስታውቋል።

መድፈኞቹ ተጨዋቾቹን ከኢኳዶሩ ክለብ ኢንዲፔንዴንቴ ዴል ቫሌ አስፈርመዋል።

መንትዮቹ በአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የሚመራው አርሰናል የረጅም ጊዜ እቅድ አካል መሆናቸው ተገልጿል።

የ 16ዓመቶቹ መንትዮች በህጉ መሰረት በ 2027 18ዓመት ሲሞላቸው አርሰናልን እንደሚቀላቀሉ ተነግሯል።

ኤድዊን ክንፍ ላይ የሚጫወት የግራ እግር ተጨዋች ሲሆን ፈጣን እና ኳስ የማነከባለል የተለየ ክህሎት የያዘ ተጨዋች ነው።

ሆልጄር በበኩሉ ቴክኒካል ክህሎት የያዘ የአጥቂ አማካይ ተጨዋች መሆኑ ተገልጿል።

@tikvahethsport   

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...