ቮዳኮም ግሩፕ በሳፋሪኮም ውስጥ 55 ከመቶ የሚደርስ የአብላጫ ድርሻ ለመያዝ ስምምነት ተፈራረሙ

Date:

የደቡብ አፍሪካው ቮዳኮም ግሩፕ በሳፋሪኮም ውስጥ 55 ከመቶ የሚደርስ የአብላጫ ድርሻ ለመያዝ የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።

ኩባንያው ከኬንያ መንግሥት እና ከዩናይትድ ኪንግደም ቮዳፎን ግሩፕ (Vodafone Group) በአጠቃላይ ስምንት ቢሊዮን አክሲዮኖችን ለመግዛት 2.1 ቢሊዮን ዶላር (272.4 ቢሊዮን ሺሊንግ) ለመክፈል ወስኗል።

በሚድራንድ (ደቡብ አፍሪካ) የሚገኘው ይህ ዓለም አቀፍ ኩባንያ በአሁኑ ወቅት በናይሮቢ የአክሲዮን ገበያ በተዘረዘረው ሳፋሪኮም ውስጥ 35 ከመቶ ድርሻ አለው። አሁን ባለው ስምምነት መሠረት፣ ቮዳኮም ስድስት ቢሊዮን አክሲዮኖችን (15% ድርሻ) ከብሔራዊ ግምጃ ቤት እንዲሁም ሁለት ቢሊዮን አክሲዮኖችን (5% ድርሻ) ከቮዳፎን ይገዛል።

ግዢው የሚካሄደው በአንድ አክሲዮን 34 ሺሊንግ በሚሆን ዋጋ ሲሆን፣ የሽያጭና ግዢ ስምምነቱ በ2026 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...

የእግር ኳስ ዳኝነት በኢትዮጵያ

ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) ግዮን መጽሔት :- እግር ኳስ...

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...