አትሌት ትግስት ግርማ ታሰረች

Date:

ከትናንት በስትያ  በተጠናቀቀው የኢትዮጵያ አትሌትክስ ሻምፒዮና በ1500ሜ ክለቧን መቻልን በመወከል 2ኛ በመውጣት ውድድራን ያጠናቀቀችው የመቻል ስፖርት ከለብ አትሌት ትዕግስት ግርማ

ለቶኪዮ የዓለም አትሌትክስ ሻፒዮና ሚኒማ ለማምጣት  ወደ ኳታር ዶሃ ዳይመንድ ሊግ በማቅናት ላይ እያለች  ነው በቦሌ አለማቀፍ አየር ማረፊያ ከክለቧ በተላለፈ ደብደቤ መሰረት የታሰረችው።

የመረጃ ምንጮቻችን እንደገለፁት የተያዘችበት ምክንያት አትሌቷ ከዚህ በፊት ክለቧን ሳታስፈቅድ ወደ አውሮፓ ለውድድር በመሄዷ ምክንያት እንደሆነ የገለፁ ሲሆን ለምን ሳታስፈቅድ ሄደች የሚል ጥያቄ  ጠይቄአቸው ነበረ ፤ለተጠየቁት ጥያቄ ሲመልሱም አትሌቷ አሰልጣኟን ጠይቃ በቃል እንደፈቀደላት ከውድድር ከተመለሰችም በኋላ ጉዳዩ እንደታየና እንደተፈታላት የገለፁ ሲሆን ከመፈታቱ በፊት በተላለፈ ደብዳቤ ምክንያት ሊሆን እንደሚችል ለኢትዮራነርስ ገልፀዋል።

ጉዳዩ የሚመለከታችሁ በሙሉ ከክለቧ ጋር በመነጋገርና ችግረሩን በመፍታት ለአትሌቷ መፍትሔ እንዲመጣና  ወደ ውድድሯ እንድታቀና አስፈላጊውን ሁሉ ትብብር እንዲደረግላት በታላቅ አክብሮት እንጠይቃለን ብለዋል የአትሌቷ የቅርብ የሆኑ የመረጃ ምንጮቻችን ።

Via Ethio Runners

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አቶ ዳውድ ኢብሳ ከምርጫው ራሳቸውን አገለሉ

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ በኦሮሚያ...

ኢራን ከአሜሪካ ጋር ‹‹ሁሉን አቀፍ ስምምነት›› እንደምትፈልግ ገለጸች

ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ጦርነት ለማቆም ከአሜሪካ ጋር በምታደርገው...

የሪል እስቴት ዘርፍ ዘመናዊ የክፍያ ቴክኖሎጂን ለማስፋፋት አዲስ አጋርነት ፈጠረ

በኢትዮጵያ የሪል እስቴት ዘርፍ ግንባር ቀደም ከሆኑት ድርጅቶች አንዱ...

የአርቲስት ጥላሁን ገሠሠ መታሰቢያ ሐውልት ተመረቀ

ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ዕድገት ወደር የሌለው አስተዋጽኦ ላበረከተውና የሙዚቃው...