አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ በተጠናቀቀው ሂሳብ ዓመት የ1.8 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማስመዝገቡን አስታወቀ

Date:

አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ በ2017 በጀት ዓመት ፈታኝ በሆነው የኢኮኖሚ ሁኔታ ውስጥ ቢሆንም የላቀ የፋይናንስና የአሠራር ውጤት በማስመዝገብ፣ ከግብር በፊት 1.8 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማግኘቱን አስታውቋል።

ይህ ትርፍ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ94% ጭማሪ ያሳየ ሲሆን፣ ባንኩ ጠቅላላ ተቀማጭ ገንዘቡ በ23% በማደግ 44.0 ቢሊዮን ብር እንደደረሰና ጠቅላላ ብድርና ቅድሚያ ክፍያው ደግሞ በ19% ጨምሮ 36.2 ቢሊዮን ብር መድረሱን ገልጿል።

የባለአክሲዮኖችን 21ኛዉ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ዛሬ ያደረገው አንበሳ ባንክ፣ የአገልግሎት ተደራሽነትን ለማሻሻል የቅርንጫፍ መረቡን በ35 አዳዲስ መውጫዎች በማስፋፋት ጠቅላላ 341 ቅርንጫፎች ያደረሰ ሲሆን፣ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽኑ ላይም ሰፊ ዕድገት አስመዝግቧል።

በዚህ አፈጻጸም የተነሳ፣ የባንኩ ጠቅላላ ንብረቶች በ25% አድገው 54 ቢሊዮን ብር ሲደርሱ፣ የተከፈለ ካፒታሉ ደግሞ በ21% በማደግ 3.7 ቢሊዮን ብር መሆኑን በዓመታዊ ሪፖርቱ አስታዉቋል።

Via Capital

@Addis_News
@Addis_News

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...