የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት (አዲስ ቻምበር) በከተማዋ ከ482 ሺህ በላይ የንግድ ፈቃድ ያላቸውን ነጋዴዎች አባል ለማድረግና አገልግሎቱን በቀላሉ እንዲያገኙ በአስራ አንዱም ክፍለ ከተሞች መዋቅሩን መዘርጋቱን አስታውቋል።
በዚህ አዲስ አደረጃጀት መሰረት በእያንዳንዱ ክፍለ ከተማ አንድ ሰብሳቢን ጨምሮ ዘጠኝ የንግዱ ማህበረሰብ ተወካዮች በአመራርነት ተመድበዋል። በተጨማሪም የምክር ቤቱን ተግባራት የሚያስተባብሩ ሰራተኞች በቅርቡ እንደሚመደቡ ተገልጿል።
ይህ አዲስ አደረጃጀት በቅርቡ ተግባራዊ እንደሚሆን ይጠበቃል፣ አላማውም አባላትን በስፋት ማሳተፍና ዘመናዊ አገልግሎቶችን ተደራሽ ማድረግ ነው ተብሏል።
