ኢራን ከአሜሪካ ጋር ለመደራደር አለመጠየቋን አስታወቀች

Date:

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋይ፤ አገራቸው ከአሜሪካ ጋር ለመደራደር ጥያቄ አለማቅረቧን ተናገሩ።

ነገር ግን ድርድር ለማድረግ ከቀጣናዊ አሸማጋይ የቀረበላቸውን ጥያቄ ተቀብለዋል። አሸማጋዮች ወደ ቴህራን አቅንተው በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት እንደሚደረግ ተናግረዋል።

“ከአሜሪካ ጋር ለመደራደር አልጠየቅንም። ሆኖም ግን ሁልጊዜም ኃላፊነት ስለሚሰማን ቀጣናዊ አደራዳሪዎችን አሻፈረኝ አላልናቸውም” ብለዋል ቃል አቀባዩ።

የመግባቢያ ሰነዱ ከተፈረመ ሳምንታት ብቻ ቢቆጠሩም “አሜሪካ ብዙ የስምምነቱን ክፍል መጣሷን” ተናግረዋል።

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ድርድሩ እንዲቀጥል መስማማታቸውን ገልጸዋል።

አሜሪካ እና ኢራን ድርድራቸውን ለመቀጠል መስማማታቸውን ትራምፕ ያሳወቁት ኳታር ከአሜሪካ ጋር በመቀናጀት አሸማጋዮችን ከአገሪቱ ባለሥልጣናት ጋር እንዲነጋገሩ ወደ ቴህራን ከላከች በኋላ ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጠቅላይ መሪ ለአባታቸው ግድያ “የበቀል እርምጃ” እንደሚወሰድ ተናገሩ

የኢራን ጠቅላይ መሪ ሞጅታባ ኻሜኒ በጽሑፍ ባስተላለፉት መልዕክት አባታቸው...

የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን የመጨረሻ ልምምዱን ሰርቷል

ቡድኑ ነገ የአለም ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ ዙር የመልስ ጨዋታውን...

ሱዳን ዉስጥ ለሦስት ዓመታት የተካሄደው ጦርነትን ሰለ ማቆም

የሱዳን ብሔራዊ ጦር ለሦስት ዓመታት የተካሔደውን ጦርነት ለማቆም አሜሪካ...

የአርሲ አሰኮ ተፈናቃዮች በርዳታ አቅርቦቶች መቋረጥ መቸገራቸውን ገለጹ

በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች ግንቦት...