የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋይ፤ አገራቸው ከአሜሪካ ጋር ለመደራደር ጥያቄ አለማቅረቧን ተናገሩ።
ነገር ግን ድርድር ለማድረግ ከቀጣናዊ አሸማጋይ የቀረበላቸውን ጥያቄ ተቀብለዋል። አሸማጋዮች ወደ ቴህራን አቅንተው በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት እንደሚደረግ ተናግረዋል።
“ከአሜሪካ ጋር ለመደራደር አልጠየቅንም። ሆኖም ግን ሁልጊዜም ኃላፊነት ስለሚሰማን ቀጣናዊ አደራዳሪዎችን አሻፈረኝ አላልናቸውም” ብለዋል ቃል አቀባዩ።
የመግባቢያ ሰነዱ ከተፈረመ ሳምንታት ብቻ ቢቆጠሩም “አሜሪካ ብዙ የስምምነቱን ክፍል መጣሷን” ተናግረዋል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ድርድሩ እንዲቀጥል መስማማታቸውን ገልጸዋል።
አሜሪካ እና ኢራን ድርድራቸውን ለመቀጠል መስማማታቸውን ትራምፕ ያሳወቁት ኳታር ከአሜሪካ ጋር በመቀናጀት አሸማጋዮችን ከአገሪቱ ባለሥልጣናት ጋር እንዲነጋገሩ ወደ ቴህራን ከላከች በኋላ ነው።
