ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን ለማስተናገድ በመመረጧ የጠቅላይ ሚኒስትሩ መልእክት

Date:

አፍሪካ በብራዚል ቤሌም ከተማ በተካሄደው የ2025ቱ የተመድ የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በአንድ ድምፅ ተናግራለች፤ ዓለምም ሰምቷታል።

የሰው ልጅ ከሚያጋጥሙት እጅግ ከባድ ተግዳሮቶች አንዱ የሆነውን ችግር ለመፍታት የሚደረገውን የጋራ ጥረት እንድንመራ ለተሰጠን ዕድልም እናመሰግናለን።

የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብም እንዲህ ያለ ወሳኝ ኃላፊነት ስለሰጠንም ክብር ይሰማናል።

ይህ እውቅና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ ባሳየችው የመሪነት ሚና እና ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ አቅሟ ላይ ያላችውን እምነት የሚያንፀባርቅ ነው።

ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 በአዲስ አበባ የሚካሄደው COP 32 ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት እንዲያስመዘግብ እና በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ እርምጃዎችን ለመውሰድ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር በቁርጠኝነት ትሰራለች።

አፍሪካ የመፍትሔ አህጉር መሆኗን እና በዓለም አቀፍ ጥረቶች ውስጥ ቁርጠኛ አጋር መሆኗን ለማሳየት ኢትዮጵያ የመሪነት ሚናዋን መጫወት ትቀጥላለችም፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...